ዘንድሮ በሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች በነፃ ለምርጫ ቅስቀሳ እንዲጠቀሙበት የተዘጋጀ የአየሮ ሰዓትና የጋዜጣ አምድ መጠን ይፋ ሆነ።
- Mar 28
- 1 min read
መጋቢት 19/2018
ዘንድሮ በሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች በነፃ ለምርጫ ቅስቀሳ እንዲጠቀሙበት የተዘጋጀ የአየሮ ሰዓትና የጋዜጣ አምድ መጠን ይፋ ሆነ።
በዚህም በራዲዮ 782.5 ሰዓት እንዲሁም በቴሌቪዥን ደግሞ 570 ሰዓት ለፖለቲካ ፓርቲዎች እና የግል እጩዎች ተዘጋጅቶላቸዋል ተብሏል።
የአየር ሰዓቱ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ወቅት ከነበረው በ10 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
በጋዜጦች ደግሞ 576 አምድ መዘጋጀቱ ተነግሯል ።
በዛሬው እለት የ7 ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የአየር ሰዓት ድልድል ዕጣ አወጣጥ ስነስርዓት እየተካሄ ነው።
በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ 24 ራዲዮ ጣቢያዎች፣ 20 ቴሌቪዥን እንዲሁም 6 ጋዜጦች የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የግል እጩዎች ፖሊሲያቸውን፣ አላማና ፕሮግራማቸውን ለህዝብ እንዲያስተዋውቁበት መመረጣቸውን ሰምተናል።
የፖለቲካ ፖርቲዎቹ እና የግል እጩዎች ከመጪው ረቡዕ መጋቢት 23 ጀምሮ እስከ ግንቦት 19/2019 ድረስ የእረፍት እና የበዓላት ቀንን ሳይጨምር ለ40 ቀናት በየመገናኛ ብዙሃኑ በሚወጣላቸው እጣ የምረጡኝ ዘመቻ ማድረግ ይችላሉ ተብሏል።
በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በራዲዮ 711 ሰዓት ለፖለቲካ ፓርቲዎች ተመድቦ የነበረ ቢሆንም የተጠቀሙት ግን 53.8 በመቶውን ብቻ እንደነበር ተነግሯል።
በተመሳሳይ በቴሌቪዥን 558.9 ሰዓት ቢመደብም ጥቅም ላይ የዋለው 60 በመቶው ብቻ መሆኑን ሲነገር ሰምተናል።
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7




Comments