top of page

ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

  • sheger1021fm
  • 3 minutes ago
  • 1 min read

ታህሳስ 11/2018

 

ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

 

የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።

 

ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚቴ በበኩሉ ምንም አይነት ድጋፍ እንደማይደረግላቸው እና ይጠብቁ እንደተባሉ ተናግሯል፡፡

 

ተፈናቃዮቹ ወደ ደብረ ብርሃን ከተመለሱ በኋላም ከዚህ ቀደም ስማቸው ተመልሰዋል በሚለው ስለተቀነሰ አሁን ከመንግስት በኩል የሚቀርብላቸው ድጋፍ የለም እንደተባሉ ያስረዳሉ፡፡

 

ተፈናቃዮቹ ቋሚ የሆነ ድጋፍ እንደሌላቸው በዚህም መቸገራቸውን ነግረውናል፡፡

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. 

 

ማርታ በቀለ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

  

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page