ኮሜርሺያል ኖሚኒስ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ተናገረ፡፡
- 2 days ago
- 1 min read
ነሐሴ 2 2018
ኮሜርሺያል ኖሚኒስ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ተናገረ፡፡

የኮሜርሺያል ኖሚኒስ የሥራ አመራር ቦርድ የኮሜርሺያል ኖሚኒስን የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድን መገምገሙን ተቋሙ ይፋ አድርጓል፡፡
በ2018 በጀት ዓመት ኮሜርሺያል ኖሚኒስ ከሚያቀርባቸው የሶስተኛ ወገን እና ሌሎች አገልግሎቶች ከ6.4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስረድቷል፡፡
በዚህም 805 ሚሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ምግኘቱን አስረድቷል፡፡
የ2018 በጀት ዓመት የገቢ እና ትርፍ እቅድ አፈጻጸም ከ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር የ14.34 በመቶ የገቢ እና የ15.4 በመቶ ያልተጣራ ትርፍ ጭማሪ አሳይቷል ብሏል፡፡
በ2018 በጀት ዓመት ከተያዘው የገቢ እና ትርፍ ዕቅድ አኳያ 94.8 በመቶ የገቢ እና 80.4 በመቶ የትርፍ ማሳካቱ ተጠቅሷል፡፡
በተያዘው በጀት ደግሞ ከ9.9 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በማግኘት ከታክስ በፊት ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ ለማትረፍ እቅድ መያዙ ተጠቅሷል፡፡
ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክና በቀድሞው ሞርጌጅ ባንክ (በኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ) ባለቤትነት በ1958 ዓ.ም የተቋቋመ የግል ኩባንያ ሲሆን፤ በሚሰጣቸው ከ13 በላይ የአገልግሎት ዘርፎች ከ45 ሺህ በላይ ሰራተኞች አሉት፡፡
ንጋቱ ሙሉ
_edited.jpg)

Comments