ከተቋማት አልፎ የግለሰቦችን የማህበራዊ ትስስር ገፅ በመጥለፍ ገንዘብ የሚሰበስቡ የዲጂታሉ ዓለም ሞጭላፊዎች ተበራክተዋል።
- Apr 21
- 1 min read
ሚያዝያ 13/ 2018
ከተቋማት አልፎ የግለሰቦችን የማህበራዊ ትስስር ገፅ በመጥለፍ ገንዘብ የሚሰበስቡ የዲጂታሉ ዓለም ሞጭላፊዎች ተበራክተዋል።
ስለ ጉዳዩ ያወሩን አንድ የጉዳቱ ተጠቂ "የስራ ስብሰባ በኦላይን (virtual meeting) ለመግባት ይህንን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ" የሚል ፅሑፍ በዋትስ አፕ አካውንታቸው እንደተላከላቸውና ማስፈንጠሪያውን እንደተጫኑት ገፃቸው ሙሉ በሙሉ በጠላፊዎች እጅ እንደገባ ይናገራሉ።
ጠላፊዎችም ትክክለኛ የማህበራዊ ትስስር ገፅ ባለቤቱን መስለው ወዳጆቻቸውን ገንዘብ እንደጠየቋቸውና እስከ መቶ ሺህ ብር ድረስ የላከላቸው ወዳጃቸው እንዳለም አውርተውናል።
ለመሆኑ እየተባባሰ ለመጣው እንዲህ ዓይነቱ የዲጂታል ዓለሙ ሙጭለፋ ለመዳን ጥንቃቄው ምን መሳይ ይሁን?
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን ጠይቀናል።
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…..
ንጋት መኮንን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7




Comments