ኢትዮጵያ የባህር በር በሰላማዊ መንገድ እንድታገኝ ቱርክዬ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ጫና እንድታደርግ ከቱርክዬ ፕሬዚዳንት ጋር ጠንከር ያለ ውይይት ማድረጋቸውን ጠ/ሚ ዐቢይ ተናገሩ።
- 19 hours ago
- 1 min read
የካቲት 11/2018
ኢትዮጵያ የባህር በር በሰላማዊ መንገድ እንድታገኝ ቱርክዬ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ጫና እንድታደርግ ከቱርኩ ፕሬዚዳንት ጋር ጠንከር ያለ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ከቱርኩ ፕሬዚዳንት ሪሲፕ ታይፕ ኤርዶዋን ጋር ሆነው በቤተመንግስት መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ኢትዮጵያ የባህር በር በሰላማዊ መንገድ ማግኘት የምትችልበት ሁኔታ ለይ ቱርክዬ በዲፕሎማሲያዊ መስኩ ጫና በመፍጠር እንዲያግዙ ከፕሬዝዳንት ኤርዶዋን ጋር ተወያይተናል ብለዋል።
ፕሬዚዳንት ኤርዶዋን ከዚህ አንፃር የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ጠንከር ያለ ውይይት አደርገናል፣ ለዚህም ምስጋና አቀርባለሁ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ከዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያ እና በቱርክዬ መካከል ያለው ዓመታዊ የንግድ ልወውጥ ቢያንስ አንድ ቢሊዮን ዶላር እንዲሞላ በሁለቱም ሀገራት ታስቦበት እንዲሰራ ከስምምነት መደረሱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል።












Comments