top of page

ኢትዮጵያ በኮቪድ እና በአጎአ መታገድ ምክንያት አብዛኛውን በሀገር የምታመርተውን ምርት መሸጥ አልቻለችም፡፡

  • sheger1021fm
  • Dec 22, 2025
  • 1 min read

ታህሳስ 13/2018

 

ኢትዮጵያ በኮቪድ እና በአጎአ መታገድ ምክንያት አብዛኛውን በሀገር የምታመርተውን ምርት መሸጥ አልቻለችም፡፡

 

ይህን ተከትሎም መንግስት አምራቾች 50 በመቶውን ለሀገር ውስጥ ፈላጊዎች እንዲሸጡት ወስኗል፡፡

 

ለመሆኑ እነዚህ ምርቶች በተለይ በኢ-ኮሜርስ የዲጂታል ገበያ እንዲቀርቡ የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሸን ምን ዓይነት ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ ነው? መመሪያና ህጋቸውንስ እንዴት እያሻሻሉ ነው?



ለመሆኑ ኢትዮ ቴሌኮም እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በኤክስፖርት የጥራት ደረጃ የተዘጋጁ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በ'ዘመን ገበያ' ለሀገር ውስጥ ሸማቾች ለማቅረብም መጀመራቸውን ተከትሎ ቅድሚያ ምን ዓይነት ስራዎች ተፈፅመው ይሆን?

 

በአለም የንግድ መስመር አንቱ የተባሉ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳትን፣ የቆዳና የቆዳ ውጤቶችን፣ የአግሮ-ፕሮሰሲንግ ምርቶችን፣ የኤሌክትሮኒክስና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ የመድኃኒትና የሕክምና ግብዓቶችን እንዲሁም ሌሎች የማኑፋክቸሪንግ ምርቶችን በዘመን ገበያ ላይም ሆነ ሌሎች የኢ -ኮሜርስ መስመሮች ላይ ለግብይት ሊቀርብ ነው ሲባል ቅድሚያ ከክፍያ ሥርዓት አንፃር ምን ተከናውኗል ተብሎ ይጠየቃል።

 

የኢ-ኮሜርስ ንግድ የተሻለ እንዲሆን አምራቾችም ምርቱን ፈላጊዎችም ተራርቀው ንግድ ቢዝነስ እንዳይበላሽ ፤ በተለይ አድካሚ የሆነውን የሎጅስቲክስ አሰራር እንዲቀየር ምን ተይዟል?

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..

ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

  

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page