top of page

አዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ለሚያስገቡ ደንበኞች የሁለት አመት የክፍያ ስርዓት ማመቻቸቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ።

  • 49 minutes ago
  • 1 min read

ሚያዝያ 21/2018


አዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ለሚያስገቡ ደንበኞች የሁለት አመት የክፍያ ስርዓት ማመቻቸቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ።


በገንዘብ እጥረት ምክንያት ለአዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ የሚያስፈልገውን ክፍያ ከፍለው አገልግሎት ማግኘት ላልቻሉ ደንበኞች የተዘረጋው ይህ አሰራር እስከ 2 ዓመት በሚደርስ የክፍያ ስርዓት እንዲከፍሉ የሚያደርግ ነው ተብሎለታል።


ተቋሙ ወደ ስራ ያስገባውን አዲስ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን የሚችሉትም የነጠላ ፌዝ ቆጣሪ ተጠቃሚ ደንበኞች ናቸው የተባለ ሲሆን የመኖሪያ ቤት እና አነስተኛ ንግድ ቤቶችን ያጠቃልላል ተብሏል።


ይህንን አሰራር የጀመርኩት ጥናትን መሰረት አድርጌ ነው ያለው አገልግሎቱ በርካታ ደንበኞቼ በገንዘብ እጥረት ምክንያት አዲስ ቆጣሪ ማስገባት መቸገራቸውን ጥናቱ አሳይቷል ብሏል።


ደንበኛው የጊዜ ገደብ ክፍያ አገልግሎቱን ተጠቃሚ ለመሆን የቆጣሪ ማስገመቻ ሙሉ ክፍያ መክፈል ያስፈልገዋል የተባለ ሲሆን ከጠቅላላ የማስቀጠያ ክፍያ ላይ 10 በመቶውን መክፈል ይጠበቅበታል ተብሏል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ……


ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Recent Posts

See All
በ"ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ዓቃቢ ህግ ክስ እንዲመሰርት 7 ቀናት ተፈቀደለት፡፡

ሚያዝያ 21/2018 በ"ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ዓቃቢ ህግ ክስ እንዲመሰርት 7 ቀናት ተፈቀደለት፡፡ በፊንቴክ ኢንቨስትመንትሽፋን በተፈጸመ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮችን ጉዳይ ለመመልከት የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page