top of page

ሐምሌ 5፣ 2016 ‘’አዩቴ ኢትዮጵያ’’ ወጣቶች በግብርናው ዘርፍ እንዲሰማሩ እየሰራሁ ነው አለ

  • sheger1021fm
  • Jul 12, 2024
  • 1 min read

ይህ የተባለው አዩቴ ኢትዮጵያ ቻሌንጅ ባዘጋጀው የስራ ፈጠራ ውድድር ላይ ነው።

 

አዩቴ ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች 555 ከግብርና ስራዎች ጋር የተገናኙ የፈጠራ ስራ ያላቸው ወጣቶች ሲያወዳድር መሰንበቱን ሰምተናል፡፡

 

ተቋሙ ኢትዮጵያ ውስጥ ግብርናው እንዲዘምንና ወጣቶች በዘርፉ እንዲሰሩ ቴክኖሎጂዎች ግብርናው ዘርፍ ላይ እንዲያዘምን እየሰራ መሆኑን ተናግሯል።

 

 ለውድድር የሚቀርቡት ቴክኖሎጂዎችና የፈጠራ ስራዎች አነስተኛ ይዞታ ባለው ማሳ ላይ የተሻለ ምርት እንዲገኝ ማድረግን ለማስቻል ነውም ተብሏል፡፡

 

ከዚህ በፊት በ2ተኛው የአዩቴ ኢትዮጵያ ውድድር አሸናፊ የነበረው የስራ ፈጠራ ሀሳብ በአህጉር አቀፍ በተካሄደው አዩቴ አፍሪካ ቻሌንጅ አሸንፏል።

 

የፈጠራ ስራው እንደ አፍሪካ የሚታየው #የአፈር_ማዳበሪያ ችግርን ይፈታል ተብሎ የታለመለት ኦርጋኒክ የአፈር ማዳበሪያ ማምረት ነው።

 

አሁን በተደረገው የ3ተኛ ዙር እዩቴ አፍሪካ ቻሌንጅ 555 የሚሆኑ የግብርናንውን ዘርፍ የሚያዘምኑ ስራዎችና የቴክኖሎጂ ሀሳቦች የቀረቡ ሲሆን በዳኞች ውሳኔ 3 ፈጠራ ስራዎች አሸናፊ ሆነዋል።

 

የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በበኩሉ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር ስራ ፈጣሪ ወጣቶች በብዛት እንዲወጡ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ተናግሯል።

 

የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በመወከል ንግግር ያደረጉት ብርሃኑ አደሬ፤ ከተባባሪዎቹ ውጪ በራሱ በ3 ዙሩ 1375 የፈጠራ ስራ ያላቸው ሰዎች በዚህ አመት ያውዳደረ ሲሆን አሁን 400 የሚሆኑት ተለይተዋል ይላሉ።

 

ከዚህ ውስጥ 50 የሚሆኑት የስራ ፈጠራዎች አሸናፊ እንደሚሆኑና ስራቸው ወደ ተግባር እንደሚገቡ ይደረጋል ብለዋል።

 

እንደ አዩቴ ያሉ ተቋማት በተለይም ግብርናው እንዲዘምን የሚያደርጉት ስራ አድንቀው በተለይም የፈጠራ ስራ እንዲስፋፋና ግብርናው እንዲዘምን እየሰሩት ያለው ስራ መንግስት ይደግፈዋል ይላሉ።

 

 ለአሸናፊዎሽም ስራቸው ወደተግባር እንደሚደረግና ከዚህ በፊት ያሸነፉት የስራ ፈጣራ ወጣቶች እየተከታተሉ መሆኑን ተናግረዋል።

 

አዩቴ ኢትዮጵያ ቻሌንጅ ላይ የሚሳተፉት እድሜያቸው ከ18 እስከ 30 ያሉ ወጣቶች ነው።

 

 አዩቴ ኢትዮጵያ ቻሌንጅ ላሸነፉ ተወዳዳሪዎች 20,000 የአሜሪካ ዶላር እንደተሸለሙ ተመልክተናል፡፡

 

በረከት አካሉ

Recent Posts

See All
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።

ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው  ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page