top of page

ነሐሴ 7፣2016 - ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርክ አሸማጋይነት፤ ሁለተኛ ዙር ንግግር መጀመራቸው ተሰማ፡፡

  • Aug 13, 2024
  • 1 min read


በሁለቱ ሀገራት መካከል የተፈጠረውን ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት ለማርገብ በቱርክ አመቻችነት ሁለተኛ ዙር ንግግር መጀመሩን የተናገሩት የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቃባይ ነብዩ ተድላ ናቸው፡፡


ቃል አቃባዩ ለሩሲያው አርቲ(RT) በሰጡት ቃለ ምልልስ ንግግሩ መጀመሩን አንጂ የተወከሉትን ዲፕሎማቶች አልጠቀሱም፡፡


በሰኔ ወር መገባደጃ ላይ በተደረገው የመጀመሪያው ዙር ንግግር ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ እና የሶማሊያ አቻቸው አህመድ ፊቅ በተገኙበት መካሄዱ ይታወሳል፡፡


ከሶማሊያ የግዛቴ አካል ነች ከምትላት ሶማሌላንድ ጋር ኢትዮጵያ በወደብ ጉዳይ የመግባቢያ ስምምነት ከፈረመች ወዲህ ሁለቱ ሃገራት የገቡበትን ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት በንግግር ለመፍታት በሰኔ ወር ላይ ያደረጉት ንግግርም ተስፋ ሰጭ መባሉ ይታወሳል፡፡


ሀገራቱ ንግግራቸውን ለመቀጠል በተስማሙት መሰረት ሁለተኛውን ዙር ንግግር እያካሄዱ መሆኑ ተሰምቷል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ።

ሐምሌ 20 2018 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ። እቅዱ የኔትወርክ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ፣ የሰብስቴሽን እና ተያያዥ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች፣ ስማርት ግሪድ እና ቆጣሪ ማስፋፋትን እንደሚያካትት አገልግሎቱ ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page