top of page

ነሐሴ 6፣2016 የድህረ ምረቃ ፕሮግራም መግቢያ ፈተና እስከ ነሐሴ10 ድረስ መራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ፡፡

  • Aug 12, 2024
  • 1 min read

ትምህርት ሚኒስቴር የድህረ ምረቃ ትምህርት ለመማር ወጥ የመግቢያ ፈተና እንደ ሀገር አቀፍ መስጠት መጀመሩ ይታወሳል፡፡


የ2017 ዓ.ም የመግቢያ ፈተናውን ለመስጠት ተማሪዎችን ለመመዝገብ ከሀምሌ 24 እስከ ነሀሴ 5 ድረስ አቅዶ የነበረ ቢሆን ዛሬ ማለዳ ባወጣው መረጃ ምዝገባው ለ5 ተጨማሪ ቀናት ተራዝሟል፡፡


ፈተናውን መውደስ የሚፈልጉ የድህረ ምረቃ ተፈታኞች እስከ ተጠቀሰው ቀን በትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በተቀመጠው ሊክ አማካኝነት መመዝገብ ይችላሉ ሲል አሳስቧል፡፡


በግልም ሆነ በመንግስት የሁለተኛ ዲግሪ አልያም ሶስተኛ ዲግሪ መማር የሚፈልጉ አመልካቾች ቅድሚያ ይህንን ፈተና ማለፍ ይጠበቅባቸዋል ሲል የትምህርተ ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡


በረከት አካሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
ኢትዮጵያ የምታመነጨው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት ደርሷል፡፡

ሐምሌ 22 2018 ኢትዮጵያ የምታመነጨው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት ደርሷል፡፡ ከዚህ ውስጥ ከውሃ የሚመነጨው ድርሻው ከ95 እስከ 96 በመቶ ነው ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያ ከውሃ በተጨማሪ እንደ ነፋስ ፣ ፀሀይ እንፋሎት ካሉና ሌሎች አማራጮች ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ሀይል በማመንጨት ስብጥሩን የማስፋት ው

 
 
 
የሐምሌ 22 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#አሜሪካ አሜሪካ እና ሳውዲ አረቢያ ኢራቅ ውስጥ በአፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች ይዞታ ላይ ድብደባ ፈፀሙ፡፡ ሰሞኑን ሳውዲ አረቢያ በኢራቅ የሚገኙ አፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች በድሮን ጥቃት አድርሰውብኛል ስትል እንደነበር አልጀዚራ አስታውሷል፡፡ ሳውዲ ጥቃቱን ከማውገዝ በተጨማሪ መበቀሌ አይቀርም በሚል ዝታ ነበር፡፡ በኢራቆቹ አ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page