top of page

ነሐሴ 26 2017 - የየመን ሁቲዎች መሪ አብዱልመሊክ አል ሁቲ የእስራኤል የአየር ጥቃት አምርረው አወገዙት

  • sheger1021fm
  • 1 hour ago
  • 1 min read

የየመን ሁቲዎች መሪ አብዱልመሊክ አል ሁቲ በርካታ ሚኒስትሮች በእስራኤል የአየር ጥቃት መገደላቸውን አምርረው አወገዙት፡፡


ባለፈው ሳምንት ሐሙስ እለት እስራኤል በየመኗ ርዕሰ ከተማ ሰንዓ በፈፀመችው የአየር ጥቃት ከተገደሉት ሹሞች መካከል ጠቅላይ ሚኒስትራቸው የነበሩት አህመድ ጋሌብ አል ራሐዊ አንዱ ናቸው መባሉን አልጀዚራ ፅፏል፡፡

ree

በእስራኤል ጥቃት የተገደሉት ሌሎች የሁቲዎቹ ሚኒስትሮች በስም ተለይተው አልተጠቀሱም፡፡


የሁቲዎቹ መሪ እስራኤልን በሚኒስትሮቹ ግድያ ያወገዙት ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ መሆኑ ታውቋል፡፡


እስራኤል የጋዛ የጦር ዘመቻዋን ከጀመረች አንስቶ ሁቲዎቹ ወደ እስራኤል ሚሳየሎች ሲተኩሱ እና አጥቂ ሰው አልባ በራሪ አካላትን /ድሮኖችን/ ሲሰዱባት ቆይተዋል፡፡


እስራኤልም እያሰለሰች በሁቲዎቹ ይዞታ ላይ ከባድ ጥቃቶችን እያደረሰችባቸው ነው፡፡


የየመንን ሰሜናዊ ክፍል የሚያስተዳድሩት ሁቲዎች የኢራን ሁነኛ የጦር እና የፖለቲካ አጋሮች መሆናቸው ይነገራል፡፡


የሁቲዎቹ አለቃ እስራኤል በሚኒስትሮቻቸው ላይ የፈፀመችውን ግድያ እንበቀላለን ማለታቸው ተሰምቷል፡፡

የኔነህ ከበደ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page