top of page

ነሀሴ 8 2017 - ከ2.6 እስከ 2.8 ሚልዮን ዓመት ያስቆጠረ የተባለ የሰው ልጅ አዲስ ቅሪተ አካል ተገኘ።

  • sheger1021fm
  • Aug 14
  • 1 min read

በአፋር ክልል ሌዲ ገራዱ አካባቢ ከ2.6 እስከ 2.8 ሚልዮን ዓመት ያስቆጠረ የአውስትራሎፒቴከስ የተባለ የሰው ልጅ አዲስ ቅሪተ አካል ተገኘ።

 

የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ የጥናት ቡድን በአካባቢው ባደረገው ምርምር 13 ጥርሶችን ያገኘ ሲሆን ዝርያውም አዲስ መሆኑን ተነግሯል።


ree

 

በአካባቢው ከዚህ ቀደም የሰው ልጅ ቅሪተ አካል ተገኝቷል ተብሏል።

 

ግኝቱም በሳይንስ ጆርናል በሆነው ኔቸር ጆርናል ላይ ታትሞ የወጣ መሆኑን ተጠቅሷል።

 

ree

አዲሱ አውስትራሎፒቴከስ ይፋዊ ስም እንዳልተሰጠው የጥናት በድን ተሳታፊ የሆኑት ፕሮፌሰር ኤም ሬክቶር ተናግረዋል።

 

አዲስ ስም ለመስጠት ተጨማሪ ቅሪተ አካል መገኘት አለበት ምርምሩም ይቀጥላል ብለዋል።

 

ree

አዲስ የተገኘው አውስትራሎፒቴከስ ዝርያ ከዚህ ቀደም ከተገኘው አውስትራሎፔቲከስ አፋሬንሲስ እንደሚለይ ተነግሯል።

 

ቅሪት አካሉ በተገኘበት አካባቢ የሰው ልጅ ከሚልዮን ዓመታት በፊት እንደሚኖርበት ጥሩ ማመሳከሪያ ነው ተብሏል።

 

በረከት አካሉ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 

 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page