top of page

ነሀሴ 7 2017 - ወጣቶች በፀጥታና በሰላም ሂደት የሚኖራቸው አቅምና ሚናን በተቋማዊ መንገድ ማሳደግ ያስፈልጋል ተባለ፡፡

  • sheger1021fm
  • Aug 13
  • 1 min read

ወጣቶች በፀጥታና በሰላም ሂደት የሚኖራቸው አቅምና ሚናን በተቋማዊ መንገድ ማሳደግ ያስፈልጋል ተባለ፡፡


የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ዛሬ በናይሮቢ ኬንያ በተከፈተው የኢጋድ የሰላም እና የፀጥታ ኮንፍረንስ ዙሪያ ወጣቶችን የጉዳዩ ባለቤት ማድረግ በተቋማዊ መንገድ ሊሆን ይገባል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡


ከአፍሪካ አህጉር 70 በመቶው ወጣት በመሆኑ የሰላምና የፀጥታ ጉዳይን ከወጣቶች ውጪ ማድረግ አይቻልም ብለዋል፡፡

ree

ያለወጣቶች ሰላምን ማሰብ አይቻላም በተመሳሳይ ያለ ሰላም ወጣቶችን ማሰብም ይከብዳል ሲሉ ዶ/ር ወርቅነህ ተናግረዋል፡፡


ኢጋድ በሰላም እና በፀጥታ ዙሪያ ላለፉት 40 አመታት ሰላምን በአባል ሀገራት ለማምጣት ብዙ ሰርቷል ይሁንና አሁንም የቀራል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡


ዶ/ር ወርቅነህ በሰላም እና ፀጥታን ከወጣቶች አንፃር ማየት ለምን ያስፈልጋል ቢባል የወጣቶች ድምፅ ካልታከለበት የእለት ተዕለት የሰላም እና የፀጥታ ስራችን ውጤታማ ስለማይሆን ነው ብለዋል፡፡


የኔነህ ሲሳይ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page