top of page

ነሀሴ 7 2017 - ወጣቶች በፀጥታና በሰላም ሂደት የሚኖራቸው አቅምና ሚናን በተቋማዊ መንገድ ማሳደግ ያስፈልጋል ተባለ፡፡

  • Aug 13, 2025
  • 1 min read

ወጣቶች በፀጥታና በሰላም ሂደት የሚኖራቸው አቅምና ሚናን በተቋማዊ መንገድ ማሳደግ ያስፈልጋል ተባለ፡፡


የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ዛሬ በናይሮቢ ኬንያ በተከፈተው የኢጋድ የሰላም እና የፀጥታ ኮንፍረንስ ዙሪያ ወጣቶችን የጉዳዩ ባለቤት ማድረግ በተቋማዊ መንገድ ሊሆን ይገባል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡


ከአፍሪካ አህጉር 70 በመቶው ወጣት በመሆኑ የሰላምና የፀጥታ ጉዳይን ከወጣቶች ውጪ ማድረግ አይቻልም ብለዋል፡፡

ያለወጣቶች ሰላምን ማሰብ አይቻላም በተመሳሳይ ያለ ሰላም ወጣቶችን ማሰብም ይከብዳል ሲሉ ዶ/ር ወርቅነህ ተናግረዋል፡፡


ኢጋድ በሰላም እና በፀጥታ ዙሪያ ላለፉት 40 አመታት ሰላምን በአባል ሀገራት ለማምጣት ብዙ ሰርቷል ይሁንና አሁንም የቀራል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡


ዶ/ር ወርቅነህ በሰላም እና ፀጥታን ከወጣቶች አንፃር ማየት ለምን ያስፈልጋል ቢባል የወጣቶች ድምፅ ካልታከለበት የእለት ተዕለት የሰላም እና የፀጥታ ስራችን ውጤታማ ስለማይሆን ነው ብለዋል፡፡


የኔነህ ሲሳይ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
የነሐሴ 8 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#የተባበሩት_አረብ_ኢሚሬትስ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ በሆርሙዝ ወሽመጥ በሁለት መርከቦቼ ላይ ጥቃት ሰንዝራለች ያለቻትን ኢራንን በብርቱ ኮነነቻት ተባለ፡፡ ኢራን በነዳጅ ጫኝ መርከቦቻችን ላይ ጥቃት ሰንዝራለች ሲል ከበድ ያለ ተቃውሞውን ያሰማው የኢሚሬትስ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እንደሆነ አልጀዚራ እና AFP ፅፈዋ

 
 
 
የቱሪዝም ተጓዥችና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የሀገርን ገፅታ በመገንባትና ቱሪዝምን ለማስተዋወቅ ከፍተኛ አስተዋጾ እንዳላቸው ይነገራል፡፡

ነሐሴ 8 2018 የቱሪዝም ተጓዥችና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የሀገርን ገፅታ በመገንባትና ቱሪዝምን ለማስተዋወቅ ከፍተኛ አስተዋጾ እንዳላቸው ይነገራል፡፡ ኢትዮጵያም ይህንን መልካም አጋጣሚ በአግባቡ ለመጠቀም እነዚህ የዘርፉ ባለሙያዎች ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡ አስፈላጊውን መረጃና ጥበቃ ማድረግ እንደሚገባ ባለ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page