top of page

ነሀሴ 20 2017 - ''ህገ ወጥ ግንባታን ለመከላከል የተሞከሩ የመፍትሔ እርምጃዎችም ብዙም ውጤታማ አልሆኑም'' ጥናት

  • sheger1021fm
  • 4 hours ago
  • 1 min read

በከተሞች አቅራቢያ ባሉ የማስፋፊያ ቦታዎች የሚካሄዱ ህገ ወጥ ግንባታዎች አልቀነሱም፡፡


ህገ ወጥ ግንባታን ለመከላከል የተሞከሩ የመፍትሔ እርምጃዎችም ብዙም ውጤታማ አልሆኑም፡፡


ይኽን ይፋ ያደረገው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ጥናት ውጤት ነው።


ህገ ወጥ ግንባታን ለመከላከል በአንድ ወቅት የማፍረስ፣ በሌላ ጊዜ ደግሞ ህጋዊ እንዲሆኑ የማድረግ የመፍትሔ እርምጃዎች እንደተሞከሩ የጥናት ውጤቱን ያቀረቡት የኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ ተመራማሪ ዶክተር ውባለም ስራው ተናግረዋል፡፡


ግን ሁለቱም መፍትሄዎች በከተሞች የሚታየውን ህገ ወጥ ግንባታ ብዙም አልቀነሰውም ብለዋል፡፡


የኢኮኖሚ ችግር፣ በህጋዊ መንገድ ቤት ለመስራት ቦታ የማግኘት ችግር ፣ እንዲሁም በመንግስት አስተዳደር ውስጥ የሚታዩ የአገልግሎት አሰጣጥ ጉድለቶች ወደ ህገ ወጥ ግንባታ ሰዎችን ከሚገፉ ምክንያቶች መካከል ተብለው ተጠቅሰዋል።


በህገወጥ ግንባታ ተሳትፈው ከተገኙና ጥናቱ ከሸፈናቸው ሰዎች ውስጥ 42 በመቶዎቹ ዕድሜያቸው ከ30 እስከ 40 ዓመት የሆናቸው ናቸው ተብሏል።


86 በመቶዎቹ ደግሞ ያገቡ መሆናቸው ተጠቅሷል።


ቁጥሩ ሰዎች በህገ ወጥ ግንባታ እንዲሰማሩ ከሚያደርጉ ምክንያቶች አንዱ ቤተሰብ መመስረት እንደሆነ ያሳያል ነው የተባለው።


በጥናቱ ከተካተቱ ሠዎች፣ ማንበብና መፃፍ የማይችሉት 13 በመቶዎቹ ብቻ ሲሆኑ 87 በመቶዎቹ እስከ መጀመሪያ ዲግሪ የሚደርስ የትምህርት ደረጃ ያላቸው መሆናቸው ተመልክቷል።


ይህም ሰዎች ስለ ህገ ወጥ ግንባታ እያወቁ ጭምር በተግባሩ እንደሚሰማሩ የሚያሳይ መሆኑ ተነግሯል ።


ንጋቱ ረጋሳ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page