ነሀሴ 2 2017 - የፕላስቲክና ጎማ አምራቾች ማህበር፤ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ድጋፍ እያደረኩ ነው ያለውን ወሬ ሀሰት ነው አለ
- sheger1021fm
- Aug 8
- 1 min read
የኢትዮጵያ ፕላስቲክና ጎማ አምራቾች ማህበር፤ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አምራቾቹ ሌላ ምርቶችን እንዲያመርቱ ድጋፍ እያደረኩ ነው ያለውን ወሬ ሀሰት ነው አለ፡፡
የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ለእነዚህ አምራቾች ድጋፍ እያደረኩ ነው፤ ከኢኮኖሚውም እንዳይወጡ እያገዝኩ ነው ይላል።
ማህበሩ በበኩሉ ይህ ስራ እንዴት የአካባቢ ባለስልጣን ሊሆን ይችላል፤ ከኢኮኖሚ እንዳይወጡ እየደገፍኩ ነው ማለቱንም አላውቅም ሲል አስረድቷል።
#የኢትዮጵያ_ፕላስቲክና_ጎማ_አምራቾች_ማህበር፤ አብዛኛው የፕላስቲክና ጎማ አምራቾች የኢንዱስትሪ ማሽኖች ሌላ ምርቶችን ተክተው የሚሰሩ አይደሉም እንደውም ከኢኮኖሚው ሙሉ በሙሉ የሚያስወጣ ነው ሲል ተናግሯል፡፡
አዋጁ ወደ ስራ ሲቀየርም በቢሊየን የወጣባቸው የኢንዱስትሪ መሳሪያዎች ለምንም አገልግሎት ስለማይውሉ እጣ ፈንታቸው የሚሆነው አውጥቶ ደጅ መጣል ብቻ ነው ሲል ማህበሩ አስረድቷል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…
ተህቦ ንጉሴ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyu.com/ycxjmm3s












Comments