ነሀሴ 15 2017 - ዛሬም ዕድሜያቸው እስከ 17 ዓመት ከሆኑ ኢትዮጵያውያን ህፃናትና ታዳጊዎች 80 በመቶዎቹ የድህነት ህይወት የሚገፉ ናቸው ተባለ።
- sheger1021fm
- Aug 21
- 1 min read
ዛሬም ዕድሜያቸው እስከ 17 ዓመት ከሆኑ ኢትዮጵያውያን ህፃናትና ታዳጊዎች 80 በመቶዎቹ የድህነት ህይወት የሚገፉ ናቸው ተባለ።
የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከአሜሪካው የጥናት ኢንስቲትዩት እና ከተባበሩት መንግስታት የህፃናት መርጃ ድርጅት ( ዩኒሴፍ ) ጋር በመሆን ያካሄደውን እና የኢትዮጵያውያን ህፃናትን የድህነት ሁኔታ የተመለከተውን ጥናት ውጤት ዛሬ ይፋ አድርጓል።
ጥናቱ ህፃናት የሚያገኙትን እንደ ምግብ፣ ጤና፣ ትምህርት፣ መጠለያ እና ንፅህና ያሉ አገልግሎቶችን በመውሰድ የተካሄደ እንደሆነ ተጠቅሷል።
ውጤቱ በኢትዮጵያ ዕድሜያቸው እስከ 17 ዓመት ከሆኑ ህፃናትና ታዳጊዎች 80 በመቶዎቹ አሁንም በድህነት ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን አሳይቷል ተብሏል።

በጎርጎሮሳዊያኑ 2018 በተካሄደ ጥናት በኢትዮጵያ የድህነት ህይወት የሚገፉ ህፃናትና ታዳጊዎች 88 በመቶ እንደነበሩ ለትውስታ ተጠቅሷል።
አሁን ላይ ከ88 በመቶ 80 በመቶ እንደቀነሰ ጥናቱ አሳይቷል ተብሏል።
80 በመቶ ድርሻም ግን ትንሽ ስላልሆነ ጉዳዩ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ሲሉ ጥናቱን ካካሄዱት ሞያተኞች አንዱ እና የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ቃለአብ ከበደ ለሸገር ሬዲዮ ተናግረዋል።
በሃያት ሬጀንሲ ሆቴል ይፋ በሆነው በዚህ የጥናት ውጤት ላይ በህፃናት ዙሪያ የሚሰሩ የተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ ድርጅቶች ተወካዮች እየመከሩበት ይገኛሉ።
ንጋቱ ረጋሳ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments