top of page

ነሀሴ 15 2017 - ኢትዮጵያ ሥርዓተ ትምህርቷን በየስንት ዓመት መከለስ እንዳለባት ያስቀመጠችው ገደብ የለም

  • sheger1021fm
  • Aug 21
  • 1 min read

ኢትዮጵያ ሥርዓተ ትምህርቷን በየስንት ዓመት መከለስ እንዳለባት ያስቀመጠችው ገደብ የለም፡፡


ሥርዓተ ትምህርትን መከለስ ሲያስፈልግ ጥናት ተደርጎ መካሄድ አለበት ፡፡


አብዛኛው ሀገራት ሥርዓተ ትምህርታቸውን በየ5 ዓመቱ የሚያሻሽሉ ሲሆን ኢትዮጵያም በቅርቡ ለዓመታት የተጠቀመችበትን ሥርዓተ ትምህርት አሻሽላ ወደ ስራ አስገብታለች፡፡


በጄኔቫ ግሎባል የትምህርት ስራ አማካሪ አቶ ሳሙኤል አስናቀ መንግስት በትምህርት ዘርፍ ማሳካት የሚፈልገውን ግብ ፣ ትውልዱ ነገ ምን ዓይነት መሰረት ይዞ ማደግ አለበት የሚለውን እቅዱን ከሚያሳይበት መንገድ አንዱ የሚዘረጋው ስርዓተ ትምህርት ነው ይላሉ፡፡


አመታትን እየጠበቀ በሚከለሰው የትምህርት ካሪኩለም ውስጥ የሚቀየሩና የማይቀየሩ ጉዳዮች ዙሪያ እንደ አለም ወጥ የሆነ ስምምነት ግን የለም ብለዋል፡፡

ree

አዲስ ወደ ስራ የገባው የኢትዮጵያ ሥርዓተ ትምህርት ዋነኛ ትኩረቱ ችግር ፈቺና አምራች ዜጋን መፍጠር ነው የሚሉት አቶ ሳሙኤል አስናቀ ይህን ወደ መሬት ለማውረድ ለትምህርት ዘርፉ አጋዥ ተደርገው ወደ ስራ የሚገቡ የቴክኖሎጂ ውጤቶችና አሰራሮች በተገቢው መንገድ ሊቃኙ ይገባል ሲሉም ይመክራሉ፡፡


ኢትዮጵያ የቀየረችው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት አንድ ተማሪ የተማረውን ትምህርት ማወቅ ብቻ በቂ ነው ብሎ አያስቀምጥም፡፡


ከተማረ በኋላ ያገኘውን እውቀት ወደ ተግባር መቀየር እንዳለበት ያስቀምጣል ብለዋል ባለሙያው፡፡


ክህሎት ያለውና ብቃትን የተላበሰ ተማሪ መፍጠር ከተቻለ ኢትዮጵያ ዓለም ላይ ተወዳዳሪ የሰው ኃይልን ማግኘት ትችላለች ሲሉም ጠቅሰዋል፡፡


ከዚህ ባለፈም ለመምህራኖች እድል መስጠትና በትምህርት ዘርፍ ላይ በሚተገበሩ ቴኮኖሎጂዎች ዙሪያ መምህሩ እንዲሰለጥን ማድረግ ይገባል የሚሉት አቶ ሳሙኤል አስናቀ የትምህርት ዘርፍ የሚጠይቀው ኢንቨስትመንት ትልቅ ነው፤ መንግስትና ህብረተሰቡ ይህን መገንዘብ አለባቸው በማለት ይናገራሉ፡፡


ሥርዓተ ትምህርቱን መሬት ላይ የሚያወርዱት መምህራን ናቸው እነሱ ላይ የሚሰራው ስራም በጥንቃቄ ታስቦና ታቅዶ ሊሆን ይገባል በማለት መክረዋል፡፡


በረከት አካሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page