top of page

ነሀሴ 15 2017 - ''ተቋማት መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆናቸውበጥናትና ምርምር ስራዎች ላይ እንቅፋት ሆነው ቀጥለዋል'' የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት

  • sheger1021fm
  • 22 minutes ago
  • 1 min read

ተቋማት መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆናቸው፣ ሰነዶችን በወጉ ሰንዶ የመያዝ ችግር እና የመሳሰሉት በጥናትና ምርምር ስራዎች ላይ እንቅፋት ሆነው ቀጥለዋል ሲል የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡


በጦርነት የወደሙ ተቋማት መረጃዎች አለመገኘትም ሌላው ችግር ሆኖ ተነሷል፡፡


የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈሪ ጥያሩ ፖሊሲዎችን በሚመለከት ኢንስቲትዩቱ በርካታ ጥናትና ምርምሮችን በማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።


ይሁን እንጂ ጥናትና ምርምሮች ያለበቂ መረጃዎችና ሰነዶች የማይከወኑ በመሆናቸው ለጥናቱ ግብአት የሚሆኑ መረጃዎችን ከተቋማት ለማግኘት ስንሄድ ለመስጠት ፈቃደኛ አይሆኑም ብለዋል።


እንደ ሀገር የመረጃ አያያዝ እየተሻሻለ ቢሆንም አሁንም ግን በርካታ ተቋማት መረጃዎቻቸውን በወጉ እየሰነዱ አይደለም ይላሉ።


አሉብን ካሏቸው ችግሮች ውስጥ ሌላኛው ደግሞ ጥናቶችን ለመከወኛ የሚሆን የገንዘብ ወይንም የበጀት እጥረት መኖር እና አሁንም በሀገሪቱ የሚስተዋለው የፀጥታ ችግር ይገኝበታል ብለዋል።


የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲቲዩት በየአመቱ በአማካይ 40 ጥናቶችን አከናውኖ እንደሚያጠናቀቅም ሰምተናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. https://www.mixcloud.com/ShegerFM/457445s/


ፍቅሩ አምባቸው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page