ነሀሴ 13 2017 - አዋኪ ድርጊት ይከወንባቸዋል የሚባሉ የንግድ ተቋማት ከት/ቤቶች ቢርቁ ይመከራል።
- sheger1021fm
- Aug 19
- 1 min read
እንደ ቁማር ቤት፣ አደንዛዥ እፅ ማስጠቀሚያ ቤቶች እና ሌሎች አዋኪ ድርጊት ይከወንባቸዋል የሚባሉ የንግድ ተቋማት ከትምህርት ቤቶች ቢርቁ ይመከራል።
ነገር ግን በአንድ በኩል #ትምህርት_ቤት ከመንገድ ሻገር ብሎ ደግሞ አዋኪ ድርጊት ናቸው ተብለው የተለዩ #የንግድ_ተቋማት ንግዳቸውን ሲያቀላጥፉ ማየት የተለመደ ነው።
ይህ ሁኔታም የተማሪዎች ሞራል እና ጤና ላይ ቀላል የማይባል ጉዳት እያደረሰባቸው መሆኑን በዳሰሳ ጥናት ተመልክቻለሁ ሲል የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ነግሮናል።
በትምህርት ቤቶች 500 ሜትር ዙሪያ ገባውን አደንዛዥ እፅ ቤት፣ ማሳጅ ቤት፣ ቁማር ቤት የመሳሰሉት መክፈት ወይም ማስጠቀም ክልክል ነው።
የአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች ታድያ ከዚህ አኳያ እንዴት ናቸው?
ፋሲካ ሙሉወርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments