top of page

ነሀሴ 13 2017 - አዋኪ ድርጊት ይከወንባቸዋል የሚባሉ የንግድ ተቋማት ከት/ቤቶች ቢርቁ ይመከራል።

  • sheger1021fm
  • Aug 19
  • 1 min read

እንደ ቁማር ቤት፣ አደንዛዥ እፅ ማስጠቀሚያ ቤቶች እና ሌሎች አዋኪ ድርጊት ይከወንባቸዋል የሚባሉ የንግድ ተቋማት ከትምህርት ቤቶች ቢርቁ ይመከራል።


ነገር ግን በአንድ በኩል #ትምህርት_ቤት ከመንገድ ሻገር ብሎ ደግሞ አዋኪ ድርጊት ናቸው ተብለው የተለዩ #የንግድ_ተቋማት ንግዳቸውን ሲያቀላጥፉ ማየት የተለመደ ነው።


ይህ ሁኔታም የተማሪዎች ሞራል እና ጤና ላይ ቀላል የማይባል ጉዳት እያደረሰባቸው መሆኑን በዳሰሳ ጥናት ተመልክቻለሁ ሲል የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ነግሮናል።


በትምህርት ቤቶች 500 ሜትር ዙሪያ ገባውን አደንዛዥ እፅ ቤት፣ ማሳጅ ቤት፣ ቁማር ቤት የመሳሰሉት መክፈት ወይም ማስጠቀም ክልክል ነው።


የአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች ታድያ ከዚህ አኳያ እንዴት ናቸው?


ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page