top of page

ነሀሴ 13 2017 - በኢትዮጵያ የደጋ አጋዘን ለማደን 15,000 ዶላር ያስከፍላል፤ ይህም ከፍተኛው የዱር እንስሳት የማደኛ ዋጋ ነው ተባለ

  • sheger1021fm
  • Aug 19
  • 1 min read

በኢትዮጵያ የደጋ አጋዘን ለማደን 15,000 ዶላር ያስከፍላል፤ ይህም ከፍተኛው የዱር እንስሳት የማደኛ ዋጋ ነው ተባለ፡፡


አንበሳን የሚያድን ሰው 4,000 ዶላር ፣ ነብር 4,600 ዶላር ይታደናል፡፡


በ2017 በጀት ዓመት ከዱር እንስሳት ህጋዊ አደን 193 ሚልየን ብር ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ተናገረ፡፡


በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ የታቀደው 200 ሚልየን ብር ነበር፡፡


ሀገሪቱ ካላት የዱር እንስሳት ሀብቷ መካከል 54 የሚሆኑትን #ህጋዊ_አደን እንዲፈጸምባቸው ትፈቅዳለች፡፡


እንደ ዝሆን፣ ዋልያ፣ አቦሸማኔ እና ቀጭኔን ጨምሮ 48 የዱር እንስሳት ደግሞ ለአደን የተከለከሉ ናቸው፡፡


በዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን የዱር እስሳት አጠቃቀም ዴስክ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ወርቁ የውጪ ሀገር አዳኝ ቱሪስቶች ወደ ሀገር ቤት ለአደን ከመጡ በኋላ የቆይታ ጊዜያቸውን እንዲያራዝሙ ለማድረግ ስራዎችን እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ree

በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማት ጥበቃና አጠቃቀምን በተመለከተ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያወጣው ደንብ ባስቀመጠው መሰረት አነስተኛው የማደኛ ዋጋ የጥርኝ ሲሆን 15 ዶላር፣ የጃርትን ደግሞ 20 ዶላር ያስከፍላል፡፡


የአየር ፊልም ቀረፃን ለማድረግ 15,000 ዶላር የሚያስከፍል ሲሆን በመሬት ቀረፃ ለማድረግ 9,000 ዶላር ይጠይቃል፡፡


ኢትዮጵያ ውስጥ ማደን የሚቻለው ያረጁ ወንድ የዱር እንስሳ ብቻ ነው ያሉን አቶ ዳንኤል ወርቁ ሴቶችና ወጣት ወንድ የዱር እንስሳት ማደን የተከለከለ ነው ብለዋል፡፡


የተከለከሉ የዱር እንስሳትን ያደነ ሰው የተቀመጠውን የማደኛ ዋጋ እጥፍ ይከፍላል ተብሏል፡፡


አፋር፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሌ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች ህጋዊ የዱር እንስሳት አደን ይካሄዳል፡፡


የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ከነባሮቹ በተጨማሪ አዳዲስ ህጋዊ የማደኛ ስፍራዎችን ለመክፈት እየሰራ መሆኑን ተናግሯል፡፡


በረከት አካሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page