top of page

ነሀሴ 13 2017 - በማሻሻያው ከ80 በመቶ በላይ ጭማሪ የተደረገው ለከፍተኛ ተከፋዮች ነው ተባለ፡፡

  • sheger1021fm
  • Aug 19
  • 1 min read

የደመወዝ ጭማሪው ለከፍተኛ ተከፋዮች ያደላ ነው፣ በማሻሻያው ከ80 በመቶ በላይ ጭማሪ የተደረገው ለከፍተኛ ተከፋዮች ነው ተባለ፡፡


በመንግስት የተደረገው የሰራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ የተለያዩ አስተያየቶችን እያስተናገደ ነው፡፡


በጉዳዮ ዙሪያ ሙያዊ ማብራሪያቸውን የሰጡን የፋይናንስ ባለሙያው አቶ ፋሲል ጣሰው ማሻሻያው መደረጉን በበጎ እንደሚመለከቱት ጠቅሰው መሆን ነበረበት ያሉትንም ነግረውናል፡፡


ዝቅተኛ ተከፋዮችን ለመደጎም ታስቦ ከሆነ በማሻሻያው እስከ 80 በመቶ የደረሰው ጭማሪ መደረግ የነበረነበት ለዝቅተኛ ተከፋዮች ነው ብለውናል፡፡


የሆነው በተቃራኒው ነው ያሉን ባለሙያው በመንግስት ይፋ የተደረገውን መሰረት አድርገው አሰላሁት ባሉት መሰረት ለዝቅተኛው ተከፋይ 26 በመቶ ሲጨመር ለከተፍተኛው ተከፋይ ደግሞ 85 በመቶ የተጨመረው ይህ መሆኑ ተገቢ አይደለም የሚል ሃሳብ አላቸው፡፡

ree

የኑሮ ጫናው ከአቅሙ በላይ ሆኖ አላፈናፍን ላለው፤ በቀን ሶስት ጊዜ መብላት ፈተና ለሆነበት የመንግስት ሰራተኛ ወደ ከፋ እጦት ውስጥ እንዳይገባ ለማድረግ መንግስት ያደረገው ጭማሪ የሚደገፍ ሆኖ፤ ነገር ግን ከግብር ነፃ የሚደረገው የገንዘብ መጠን ከዝቅተኛው ደሞዝ ጀምሮ ወደታች ያለው የገንዘብ መጠን ሊሆን እንደሚገባ መታሰብ እንዳለበት ያነሳሉ፡፡


ለአብነትም በዚህ ማሻሻያ ዝቅተኛው ደመወዝ 6 ሺህ ብር ከሆነ ከግብር ነፃ መሆን የነበረበትም 6ሺህ ብር ነው፤ዝቅተኛውን ደመወዝ ከግብር ካላስወጣነው ዝቅተኛ ተከፋዩን ከኢኮኖሚ ጫና ማላቀቅ አንችልም ይህ መታሰብ አለበትም ብለዋል፡፡


ከመጪው መስከረም ጀምሮ ተግባራዊ ለሚደረገው የደመወዝ ማሻሻያ 160 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ገንዘብ ወደ ኢኮኖሚው ስለሚገባ የዋጋ ግሽበቱን ሊያባብሰው ይችላል የሚሉ ባለሙያዎችን ሃሳብ እንደማቀበሉት የሚናገሩት የፋናንስ ባለሙያው አቶ ፋሲል፤ ገንዘቡ የሚከፈለው ምርታማ ለሆኑ ሰራተኞች በመሆኑ የበለጠ ምርታማነትን ይጨምራል እንጂ በራሱ የዋጋ ግሽበትን አያመጣም፤ ይህ ሲባል ግን የኢኮኖሚ አሻጥር የሚፈጥር ካለ የተፈራው ነገር መከሰቱ አይቀርም ለዚህም ቁጥጥር ያስፈልጋል ባይ ናቸው ባለሙያው፡፡


የደመወዝ ማስተካከያው የማይመለከታቸው በግሉ ዘርፍ ያሉ ተዋንያን ለምርታማነታቸው ማደግ ፤ በስራ ገበያው ላይ የሚገጥማቸውን ከፍተኛ ውድድር ለመቋቋም ሲሉ አቅማቸውን ያገናዘበ የደመወዝ ማስተካከያ ስለማድረግ ማሰብ አለባቸው ሲሉ መክረዋል፡፡



ምንታምር ፀጋው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page