top of page

ነሀሴ 12 2017 - ከኢትዮጵያ ህዝብ 46 በመቶ ያህሉ አሁንም ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ተራርቆ የሚገኝ ነው ተባለ።

  • sheger1021fm
  • Aug 18
  • 1 min read

በኢትዮጵያ እስካሁን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማቅረብ የተቻለው ለ54 በመቶ ህዝብ መሆኑ ተነግሯል።


ከመደበኛው የሃይል መስመር ለሁሉም ዜጋ የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ማዳረስ በተለያየ ችግር ምክንያት የማይቻል እንደሆነ ተነግሯል።


የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች ሲናገሩ እንደሰማነው መንግስት ከአምስት ዓመት በኋላ በጎርጎሮሳዊያኑ አቆጣጠር 2030 ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከቤቱ የኤሌክትሪክ ብርሃን እንዲኖረው የማድረግ ግብን አስቀምጧል።


ይህን ግብ ግን ደንበኛውን ከመደበኛው የሃይል መስመር በማገናኘት ብቻ ማሳካት የሚቻል ስላልሆነ 65 በመቶውን ከመደበኛው የሃይል መስመር፣ ቀሪውን 35 በመቶ ደግሞ መደበኛ ካልሆነ አነስተኛ የሃይል ማግኛ አማራጭ እንዲሸፈን ይደረጋል ነው የተባለው።

ree

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታው ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መስመርን በመደበኛ የሃይል አማራጭ ሙሉ ለሙሉ ለመሸፈን እንዳይቻል የሚያደርገው ምክንያት ብዙ ነው ብለዋል።

የአቅምና የገንዘብ እጥረት ችግር አንደኛው ፈተና ነው ያሉት ሀላፊው ይህ በሚበዙት የአፍሪካ ሀገራት ያለ ችግር መሆኑን አብራርተዋል።


በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ እንደውም ከብዙዎቹ በተሻለ ደረጃ ላይ ነች ብለዋል።


ሌላኛው በኢትዮጵያ ያለው የተበታተነ ዓይነት ያሰፋፈር ሁኔታ ስራውን ከባድ አድርጎታል ያሉት ሀላፊው የተራራቀና የተበታተነ አሰፋፈር ባለበት ሀገር መሰረተ ልማትን ማዳረስ በጣም ከባድ ነው ሲሉ አስረድተዋል።


ሌላኛው የኢትዮጵያ የመሬት አቀማመጥ ተራራማ መሆን በችግርነት የሚነሳ ምክንያት ነው ብለዋል።


እነዚህ ሶስት ምክንያቶች የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ከመደበኛው መስመር ለሁሉም ማዳረስን ከባድ ያደርጉታል ብለዋል።


በእነዚህ ችግሮች ምክንያት 35 በመቶ ከመደበኛው የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ብዙ ርቆ የሚገኘው ህዝብ ኤሌክትሪክ የሚያገኘው አነስተኛ ግድቦችን በመገንባት እና እንደ የፀሀይ ሃይል ካለው ታዳሽ የሃይል አማራጭ ይሆናል ተብሏል።


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትም እስካሁን ከፀሀይ ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ከሰራቸው ስራዎች 8 ሜጋ ዋት ሀይል ማግኘቱን ተናግሮ ከ100 በላይ ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች ደግሞ በግንባታ ላይ መሆናቸውን ነግሮናል።


ቴዎድሮስ ወርቁ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

ታህሳስ 6 2018 በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ቡሣ ጎኖፋ ወይም የእርዳታ ማስተባበሪያ በበኩሉ ድጋፍ እንዲቀጥል ለሚመለከተው የበላይ አካል ባሳውቅም ድጋፍ ግን ሊቀጥል አልቻለም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page