ነሀሴ 12 2017 - መንግስት ከመጪው መስከረም ወር ጀምሮ ለሰራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ እንደሚደርግ ተናገረ
- sheger1021fm
- Aug 18
- 1 min read
በዚህም መሰረት ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4,760 ወደ ብር 6,ዐዐዐ ብር ፣ ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21,492 ወደ ብር 39,000 ብር እንዲሆን ተወስኗል፡፡
የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ደግሞ ከብር 6,940 ወደ 11,500 ብር እንዲያድግ ይደረጋል ብሏል።

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ይህ ማሻሻያ መንግስትን ተጨማሪ 160 ቢሊዮን ብር የሚጠይቅ እንደሆነ አስረድቷል፡፡
በዚህም ኢትዮጵያ ለደመወዝ የምታወጣው ዓመታዊ ወጪ ወደ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል ተብሏል፡፡
የደመወዝ ጭማሪ ካለው የልማት ፍላጎት አንጻር አገልግሎቶችና መሠረተ ልማት ለማስፋፋት የሚያስፈልገውን ሀብት የሚሻማ ቢሆንም፣ የመንግሥት ሠራተኛውን ኑሮ ማሻሻል ቅድሚያ የሚሰጠው በመሆኑ የተወሰነ ነው ብሏል የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን፡፡
ይሄ የመጨረሻ ማሻሻያ አንዳልሆነ የተናገረው መንግስት በቀጣው ሪፎርሙ እየታየ ጭማሪ የሚደረግ ይሆናል ሲል አስረድቷል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments