top of page

ዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ ከደንበኞቼ በአደራ መልክ የሰበሰብኩትን 16.9 ሚሊየን ብር ለግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ድጋፍ አደረግሁ አለ።

  • 4 hours ago
  • 1 min read

ሚያዝያ 24/2018


ዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ ከደንበኞቼ በአደራ መልክ የሰበሰብኩትን 16.9 ሚሊየን ብር ለግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ድጋፍ አደረግሁ አለ።


30ኛ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ ባንኩ ባዘጋጀው ዳሸን ኤክስፖ የማጠናቀቂያ መርሐ ግብር፤ የዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ የ8 ዓመት የስኬት ጉዞን አስመልክቶ ማብራሪያ ተሰጥቷል።


በመርሐ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት በዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ቺፍ ኦፊሰር አቶ አምዱ ሰማን ባንኩ ጠንካራ የሸሪዓ አማካሪ ኮሚቴ በማቋቋም የማህበረሰቡን ዕሴቶች ያከበሩና ሸሪዓውን የጠበቁ አገልግሎቶች መስጠቱን አጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።



የዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት 'ሸሪክ' ከሚሰጣቸው ዘመናዊና አካታች የባንክ አገልግሎቶች ባሻገር ማህበራዊ ሐላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝም ያነሱት አቶ አምዱ በዛሬው ዕለት ለግብረ-ሰናይ ድርጅቶች የተሰጠው የገንዘብ ድጋፍ የዚሁ ተግባር አንድ አካል መሆኑን አንስተዋል።


ሸሪክ በዚህ ስምንት ዓመት ውስጥ ከ1.5 ሚሊየን በላይ ደንበኞችን ማፍራት እንደቻለ እና ከ25 ቢሊየን ብር በላይ ተቀማጭ ማድረሱን ባንኩ ተናግሯል።


የዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት 'ሸሪክ' ከ17 ቢሊየን ብር በላይ የተለያዩ ዘርፎችን ፋይናንስ ማድረግ ችሏልም ተብሏል።


ባንኩ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ አሁን ላይ ከ90 በላይ በሆኑ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነጻ የሆኑ ቅርንጫፎች እና በሁሉም የዳሸን ባንክ ቅርንጫፎቼ በመስኮት በኩል አገልግሎቱ እየተሰጠሁ ነው ብሏል።


ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page