ዘንድሮ 34 የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቅቆ እንደሚመረቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተናገረ፡፡
- 16 minutes ago
- 1 min read
ሚያዝያ 24/2018
ዘንድሮ 34 የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቅቆ እንደሚመረቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተናገረ፡፡
ከ500 በላይ የመንገድ ፕሮጀክሮችን እየሰራ መሆኑን የሚጠቅሰው አስተዳደሩ ከግማሽ በላዩ እየተሰሩ ያለው በሃገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች ነው ብሎናል፡፡
አንዱና አካባቢ ከሌላው ገጠሩን ከከተማው የሚያገኛኙ የመንገድ ግንባታዎች፣ ጥገናዎችና የዲዛይን ስራዎች እየተሰራባቸው ያሉ ከ500 በላይ ፕሮጀክቶች እንዳሉ የነገሩን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሃመድ አብዱራህማን፣ ከእነዚህ መካከል የፈጣን መንገዶችን፣ ክልሎችን እርስ በስርስ የሚያገናኙ፣ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ተነስተው በ5 አቅጣጫ የሚወጡ ፕሮጀክቶች ናቸው ብለውናል፡፡
ለመሆኑ የኢትዮጵያ የመንገድ ሽፋን ምን ያህል ደርሷል?ያልናቸው ሃላፊው ከ24ዓመታት በፊት 26 ሺህ ኪሎ ሜትር የነበረው የኢትዮጵያ የመንገድ ሸፋን አሁን 180 ሺህ ኪሎ ሜትር ደርሷል፤ከዚህም ውስጥ 30 ሺህ ኪሎ ሜትሩ በፌድራል ደረጃ ያለ ነው ብለዋል፡፡

በዘንድሮ ዓመትም በመላው ኢትዮጵያ እየተገነቡ ያሉ 34 የመንገድ ፕሮጀክቶች ስራቸው ተጠናቅቆ ይመረቃሉ ሲሉም ያስረዳሉ፡፡
ከዚህ ቀደም የመንገድ ግንባታን ጨምሮ በአጠቃላይ የግንባታው ዘርፍ የስራ ተቋራጮችና አማካሪ መሃንዲሶች በውጭ ምንዛሪ ከሌሎች ሃገራት መጥተው የሚሰሩ ነበሩ የሚሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሃገር ቤት ባለሙያዎቻችን አቅም በብዙ መንገድ እየተገነባ በመሆኑ ከግማሽ በላይ እስከ 55 በመቶ የሚሆኑ ስራዎቻችንን በእነዚሁ ባለሙያዎች ነው የምናሰራው፤እንደውም ሙሉ በሙሉ በራሳችን ባለሙያዎች የመስራት ውጥን አለን ሲሉም ያስረዳሉ፡፡
እየተገነቡ ያሉ እነዚህ የመንገድ ፕሮጀክቶች በወሰን ማስከበር ችግሮች፣ በግንባታ እቃዎች መወደድና፣ በግጭቶች ምክንያት ፈተና ውስጥ ቢሆንም ስራቸው ተቋርጦ የነበሩ 14 የመንገድ ፕሮጀክቶችን በዚህ ዓመት ስራቸውን እንደገና ማስጀመሩን መናገሩ ይታወሳል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments