ነሀሴ 10 2017 - ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የ30 ዓመታት ጉዞውንና የወደፊት ሀሳቡን የሚያሳይበት ዓውደ ርዕይ ማዘጋጀቱን ተናገረ
- sheger1021fm
- Aug 16
- 1 min read
45 ድርጅቶችን በስሩ የሚያስተዳድረው ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የባለፉትን 30 ዓመታት ጉዞውንና የወደፊት ሀሳቡን የሚያሳይበት ዓውደ ርዕይ ማዘጋጀቱን ተናገረ።
ዓውደ ርዕዩም ከነሃሴ 26/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 5 ቀናት በሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ ተነግሯል።
በዝግጅቱ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎቶታቸውን ይዘው ይቀርባሉ፣ የገበያ ትስስር ይፈጥራሉ፣ ለማህበረሰቡም ይሸጣሉ ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪም ሚድሮክ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ያበረከተው አስተዋጽኦ በተመለከተ በምጣኔ ሀብት አዋቂዎች የፓናል ውይይት እንደሚካሄድ ተነግሯል።
የዓውደ ርዕዩ ዋና አላማም የሜድሮክን ስኬቶች ማሳየት፣ከህዝቡ ጋር ያለውን ግኑኝነትም ለማጥበቅ እንዲሁም የወደፊት እቅዶቹን ማሳወቅ መሆኑ ተጠቅሷል።
45 ኩባንያዎች ያሉት ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በሆቴልና ቱሪዝም፣ በአገልግሎት፣ በኮንስትራክሽን በመሳሰሉት ዘርፎች ይሰራል።
ግሩፑ በየዓመቱ ከሚያገኘው ትርፍ 10 በመቶው ማህበራዊ ሀላፊነቱን ለመወጣት ለተለያዩ ማህበረሰብ አቀፍ አቀልግሎት እንደሚያውለው ተነግሯል።
ንጋቱ ሙሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments