ነሀሴ 1 2017 - ለፕላስቲክ አምራቾች፤ ድጋፍ እያደረግንላቸው ነው ሲል የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ተናገረ
- sheger1021fm
- Aug 7
- 1 min read
ፕላስቲክ አምራቾች፤ የተከለከሉ የፕላስቲክ ከረጢቶችን የሚተካ ሌላ ምርቶችን እንዲያመርቱ ድጋፍ እያደረግንላቸው ነው ሲል የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ተናገረ።
ባለስልጣኑ ከዚህ ቀደም አንድ ጊዜ ጥቅም ላይ ውለው የሚጣሉ ፕላስቲኮችን የሚያመርቱ ፕላስቲክን የሚተኩ ምርቶች ላይ ቢሰማሩ የኢኮኖሚ ችግር አይገጥማቸውም ብሏል፡፡
በቅርቡ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፀደቀው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ ላይ #የፕላስቲክ_ፋብሪካዎች ይዘጉ፣ ፕላስቲክን ሙሉ በሙሉ አትጠቀሙ የሚል ነገር አልተቀመጠም አዋጁ የከለከለው አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ ውለው የሚጣሉ የፕላስቲክ ከረጢቶችን ነው ብሏል ባለስልጣኑ።

ባለስልጣኑ ይህን ቢልም የኢትዮጵያ ፕላስቲክ እና ጎማ አምራቾች ዘርፍ ማህበር አንድ ጊዜ ጥቅም ላይ ውሎ የሚጣል የፕላስቲክ ከረጢት የለም ማለቱን ከዚህ ቀደም ዘግበን ነበር።
አቶ ዲዳ ድሪባ የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ናቸው።
በቅርቡ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፀደቀው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ ታትሞ ወደ ባለስልጣኑ ሲመጣ የተደነገጉ ድንጋጌዎችን ለማስፈፀም መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ያሉ ብክለቶችን ለመቀነስ እንደ ባለስልጣን መስሪያ ቤት በርካታ ስራዎችን እየከወንን ነው ያሉት አቶ ዲዳ ሆኖም በከተማዋ ለረዥም ዓመት የቆየ ከፍተኛ የብክለት ክምችት በመኖሩ የሚፈለገውን ያህል ውጤት እንዳናመጣ አድርጎናል ብለዋል።
ፍቅሩ አምባቸው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyu.com/ycxjmm3s












Comments