top of page

ከዶላር አንፃር የብር የመግዛት አቅም በአንድ ብር ከ 50 ሳንቲም ተጠናከረ፡፡

  • 1 hour ago
  • 1 min read

ነሐሴ 14 2018


ከዶላር አንፃር የብር የመግዛት አቅም በአንድ ብር ከ 50 ሳንቲም ተጠናከረ፡፡


የኢትዮጵ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው የግማሽ ብሊዮን ዶላር ጨረታ የአንድ ዶላር አማካይ የመግዣ ዋጋ 160 ብር ከ21 ሳንቲም ሆኗል፡፡





ይህም ባለፈው ሳምንት በነበረው ጨረታ አንድ ዶላር ከተሸጠበት 161 ብር ከ75 ሳንቲም አማካይ ዋጋ ጋር ሲነፃፀር ዛሬ የብር መግዛት አቅም መጠነኛ መጠናከር አሳይቷል፡፡


በዛሬው የጨረታ በልዩ ሁኔታ 5 መቶ ሚሊዮን ዶላር የቀረበ ሲሆን የባንኮች ፍላጎት ከ710 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንደነበር ከባንኩ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡


በጨረታው 22 ባንኮች ተሳትፈው ከአንድ ባንክ ውጪ ሁሉም የተለያየ መጠን ያለው ዶላር እንደገዙም መረጃው ያሳያል፡፡


የዛሬውን ጨምሮ 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በጨረታ ለባንኮች ያቀረበው ብሔራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሬ ገብያውን በታቀደው ልክ ማረጋጋት የተቻለ አይመስልመ፡፡


የብር የመግዛት አቅም በየጊዜው እየተዳከመ ሲሆን ጥቁር ገብያውና በመደበኛው የውጭ ምንዛሬ ገብያ መካከል ያለው ልዩነት ከ15 ከመቶ በላይ ሆኖ መቀጠሉ ይነገራል፡፡


ትዕግሥት ዘሪሁን

Recent Posts

See All
ባለፉት ጊዜያት በነበረው የ12ኛ ክፍል የተማሪዎች ውጤት ዝቅ ማለት «ተማሪዎች የመማር ፍላጎታቸው እየቀነሰ ነው» የሚል ሀሳብ ሲነሳ ይደመጣል።

ነሐሴ 14 2018 ባለፉት ጊዜያት በነበረው የ12ኛ ክፍል የተማሪዎች ውጤት ዝቅ ማለት «ተማሪዎች የመማር ፍላጎታቸው እየቀነሰ ነው» የሚል ሀሳብ ሲነሳ ይደመጣል። በሌላ በኩል ደግሞ ይህ የፈተና ስርዓት ጥብቅ መሆኑ ተማሪዎችን የበለጠ በራሳቸው እንዲተማመኑ እያደረገ ነው የሚል ሃሳብ ከሌላኛው ወገን ይነሳል። አሁን በ

 
 
 
በኢትዮጵያ ሥርዓተ ምግብን፣ የአየር ንብረት ለውጥንና ሥርዓተ ጾታን የተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ሥራዎች አንዱ ከአንዱ ጋር ተናበው የሚከወኑ ባለመሆናቸው ውጤት ከማምጣት ይልቅ ችግሩን ውሃ ቅዳ፣ ውሃ መልስ አድርጎታል ተባለ።

ነሐሴ 14 2018 በኢትዮጵያ ሥርዓተ ምግብን፣ የአየር ንብረት ለውጥንና ሥርዓተ ጾታን የተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ሥራዎች አንዱ ከአንዱ ጋር ተናበው የሚከወኑ ባለመሆናቸው ውጤት ከማምጣት ይልቅ ችግሩን ውሃ ቅዳ፣ ውሃ መልስ አድርጎታል ተባለ። ሥርዓተ ምግብና የአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዘው የሚከሰቱት ችግሮች ተጽዕኗ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page