top of page

ታህሳስ 7፣ 2015- የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ በሀላፊነት ላይ የሚገኙትን ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሣን በፍርድ ቤት መክሰሳቸው ተሰማ


የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ በሀላፊነት ላይ የሚገኙትን ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሣን በፍርድ ቤት መክሰሳቸው ተሰማ፡፡


ዙማ በጆሃስበርግ ፍርድ ቤት በግል በራማፎሣ ላይ ክስ መመስረታቸውን በስማቸው የተቋቋመ ድርጅት እወቁልኝ ማለቱን ዘ ሳውዝ አፍሪካን ፅፏል፡፡


ጉዳዩ ከፋላ ፋላው አጋጣሚ ጋር የተገናኘ ነው ተብሏል፡፡


ከፕሬዝዳንቱ የፋላ ፋላ እርስት በውጭ ምንዛሪ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ መዘረፉን ሸፋፍነዋል በሚል ሪፖርት ከወጣ በኋላ ራማፎሣ ጫና በርትቶባቸው ሰንብቷል፡፡


ፕሬዝዳንት ራማፎሣ የዙማን ክስ አይረቤ እና መሰረተ ቢስ ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


በደቡብ አፍሪካ የገዢው የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ ANC የፖለቲካ ማህበር አገራዊ ሸንጎ ዛሬ መሪውን ይመርጣል ተብሏል፡፡


በጫና ውስጥ የከረሙት ሲሪል ራማፎሳ አንዱ ተፎካካሪ መሆናቸው ታውቋል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


bottom of page