top of page

ታህሳስ 24፣2017 - አካል ጉዳተኞችን በሁሉም አገልግሎቶችና ስራዎች ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ ሊሰራበት ይገባል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Jan 2
  • 1 min read

አካል ጉዳተኞችን በተመለከተ ሊጠበቁላቸው ከሚገቡ መብቶቻቸው ውስጥ በሁሉም አገልግሎቶችና ስራዎች ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ ሊሰራበት ይገባል ተባለ፡፡


በተለይ አካል ጉዳተኞች በጥበብ ስራዎች ላይ የሚከውኗቸው ስራዎች የላቁ ቢሆኑም ተመልካች አገኝተው ወደ እውቅና ዘርፍ የሚመጡት ጥቂቶችን እንደሆኑ ተነግሯል፡፡


ዓለም አቀፉን የአካል ጉዳተኞች ቀን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንና ከዓለም ጋለሪ ጋር በመተባበር በተሰናዳ ኤግዚቢሽን የአካል ጉዳተኞችን መብቶች ማስከበር ላይ የተከወኑ ካሉ ስራዎች በአካል ጉዳተኞች የሚሰናዱ የጥበብ ስራዎችን መደገፍ አንዱ እንደሆነ ተነግሯል፡፡


ree

ree

በኢግዚቢሽኑ ላይ በተለያየ የሙያ መስክ የተሰማሩና አካል ጉዳተኛ የሆኑ ባለሙያዎች የተሳተፉበት ሲሆን ስለ ጥበብ ስራዎቻቸውም ነግረውናል፡፡


በኤግዚቢሽኑ ላይ የቀረቡት የስዕል ስራዎች አካል ጉዳተኞች የሚገጥሟቸው የተለያዩ ፈተናዎች እንዲሁም ተስፋዎች ያንፀባረቁበት ነው፡፡


60 አካል ጉዳተኞች የስዕል ስራዎቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን በኢግዚቢሽኑ ከተሳተፉት መካከል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሴቶች ህፃናት አካል ጉዳተኞችና አረጋዊያን መብቶች ኮሚሽነር የሆኑት ርግብ ሐዋሪያ አንዷ ናቸው፡፡


ree

ree

የአካል ጉዳተኞች መብቶችን በተለይ ደግሞ አካል ጉዳተኞች በተለያዩ ዘርፎች የሚያጋጥሟቸውን መሰናክሎች የሚያሳዩ ብዙ ስዕሎች አሉ፡፡ በስራውም ተሳትፌአለሁ ብለዋል፡፡


በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዓለማቀፉን የአካል ጉዳተኞች ቀን አስመልክቶ በተሰናደው የስዕል ኤግዚቢሽን የተለያየ የአካል ጉዳት ያለባቸውና በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የተሰማሩ ባለሙያዎች የተካፈሉበት ሲሆን እስከ ጥር 6 2017 ዓ.ም እንደሚዘልቅና ለጎብኚዎቹም ክፍት መሆኑን ሰምተናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… https://tinyurl.com/2brw7n5u


ምህረት ስዩም


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page