ታህሳስ 17፣2017 - የንብረት ታክስ ትመና የከተሞችን ዓመታዊ ወጪ ፍላጎት ከግምት ውስጥ በማስገባት የሚሰላ ነው ተባለ
- sheger1021fm
- Dec 26, 2024
- 1 min read
የንብረት ታክስ ትመና የከተሞችን ዓመታዊ ወጪ ፍላጎት ከግምት ውስጥ በማስገባት የሚሰላ ነው ተባለ፡፡
ይህ የተባለው በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ #የንብረት_ታክስ ረቂቅ አዋጅ ላይ በተደረገ ውይይት ወቅት ነው፡፡
የንብረት ታክስ ከሌሎች የታክስ ዓይነቶች የሚለየው ግብር ከፋዩ ይህን ያህል መክፈል እችላለሁ ብሎ የሚያቀርበው ሳይሆን በከተሞች ውሳኔ ተተምኖ ሚሰበሰብ ነው ተብሏል፡፡

ረቂቁ ለቋሚ ኮሚቴው አባላት ያቀረቡት የገንዘብ ሚኒስቴር የህግ ጉዳዮች መመሪያ ኃላፊ አቶ ተወዳጅ መሃመድ ናቸው፡፡
የንብረት ታክስ ( #Property_Tax ) በሊዝ ይዞታ በሚተዳደር መሬት የሚጠቀም መብት ላይ በቤት በህንፃ እንዲሁም በመሬት ማሻሻያ ላይ የሚጣል እንደሆነ አቶ ተወዳጅ አስረድተዋል፡፡
ሌሎች ሀገራት ተንቀሳቃሽ ንብረቶች ላይ የንብረት ታክስን እንደሚጥሉ ያስረዱት ኃላፊው ኢትዮጵያ ግን ተሽከርካሪን ወይም ተንቀሳቃሽ ንብረት ላይ ታክሱን ተግባራዊ እንደማታደርግ አስረድተዋል፡፡
በአዋጁ ለአንድ ሰው መኖሪያነት ሚያገለግል ቤት ታክስ እንደማይደረግ ተነግሯል፡፡
ይህ ግን በአዋጁ በግልፅ አንድ የሰው መኖሪያ ማለት ምን ማለት ነው? የሚለው በግልፅ ትርጓሜ አልተሰጠውም፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…
ያሬድ እንዳሻው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il











Comments