top of page

በኢትዮጵያ በታክስና ግብር ስወራ፣ በሙስና፣ በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ በኦንላይን ማጭበርበር እና ከሌሎች ከባድ ወንጀሎች ጋር ግንኙነት አለው የተባለ በቢሊየን ብር የሚቆጠር ንብረት መታገዱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።

  • 6 hours ago
  • 2 min read

ነሐሴ 12 2018


በኢትዮጵያ በታክስና ግብር ስወራ፣ በሙስና፣ በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ በኦንላይን ማጭበርበር እና ከሌሎች ከባድ ወንጀሎች ጋር ግንኙነት አለው የተባለ በቢሊየን ብር የሚቆጠር ንብረት መታገዱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።




በ2018 ዓ.ም ብቻ በተከናወነ የምርመራና የሕግ ማስከበር ሥራ፣ በ544 የክስ መዝገቦች ሥር የተካተቱ በርካታ ሀብቶች ታግደው የሕግ ሂደታቸውን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ ተብሏል።


በዚህም መሠረት ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ፣ ዋጋቸው ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ አክሲዮኖች፣ ከ5 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት፣ ከ200 በላይ ቤቶች፣ ከ300 በላይ ተሽከርካሪዎች እና 69 ከባድ ማሽነሪዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና እንዲታገዱ መደረጉን ሰምተናል።


ሥራ ላይ ከዋለ ከአንድ ዓመት በላይ የሆነው አዋጁ የሕገ-ወጥ ሀብት ምንጭን በጥብቅ በመመርመርና በማረጋገጥ፣ ንብረቱ ለመንግሥትና ለሕዝብ ጥቅም የሚወረስበትን ግልጽ ሕጋዊ አሰራር ዘርግቷል።


ሕጉ በጸደቀበት ወቅት እስከ 10 ዓመት ወደ ኋላ ተመልሶ ተጠያቂነት እንዲኖር መፍቀዱ በበርካቶች ዘንድ ከፍተኛ ክርክር አስነስቶ እንደነበር ይታወሳል።


በተለመደው የሕግ አሰራር አንድ ንብረት በሕገ-ወጥ መንገድ መገኘቱን ማስረዳት ያለበት ከሳሽ አካል ቢሆንም፤ በዚህ አዋጅ መሠረት ግን «ሀብቴ በሕጋዊ መንገድ የተገኘ ነው» ብሎ የማሳመንና የማስረዳት ሸክሙ ሙሉ በሙሉ የተከሳሹ ነው።


አዋጁ የታወቀ የገቢ ምንጭ ያላቸው ሰዎች ከሚያገኙት ገቢ ጋር ያልተመጣጠነና የተጋነነ የሀብት ልዩነት ሲገኝባቸው ወይም ምክንያታዊ ጥርጣሬ ሲኖር ምርመራ እንዲደረግባቸው ይደነግጋል።


በተመሳሳይ የታወቀ የገቢ ምንጭ የሌላቸው ግለሰቦች ያፈሩትን ሀብት እንዴትና በምን መንገድ እንዳጠራቀሙት ማስረዳት ካልቻሉ፣ ምርመራ ተካሂዶ ክስ በመመሥረት ንብረቱ እንዲወረስ ያዝል።


በጠቅላይ ዐቃቤ-ሕግ የሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ኃይሌ የአዋጁ ዋና ዓላማ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘን ሀብት መለየት፣ መመርመር፣ ማገድና የፍርድ ቤት ሂደቱ ሲጠናቀቅ ደግሞ ሙሉ በሙሉ መውረስ እንደሆነ አስረድተዋል።


በ2018 ዓ.ም የታገዱት ጥሬ ገንዘቦች፣ አክሲዮኖች፣ መሬቶችና ሌሎች ንብረቶች ከጀርባቸው ትላልቅ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ወንጀሎች ያሉባቸው እንደሆኑ የጠቆሙት ምክትል ዳይሬክተሩ፣ የወንጀል ጉዳዮቹ በሕግ ሂደት ውሳኔ ሲያገኙ የውርስ አቤቱታው በይፋ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።


የሀብት ማስመለስ አዋጁ ትግበራ ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል የተባለ ሲሆን፣ ሰሞኑንም የሀገሪቱን የፋይናንስ ሥርዓት የሚያናጉ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ 169 ግለሰቦች እንዲሁም በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ የተጠረጠሩ 109 ግለሰቦች ተለይተዋል።


ከእነዚህም መካከል እስካሁን 91 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ...




ገዛ ጌታሁን

Recent Posts

See All
የነሐሴ 12 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሩሲያ የሩሲያው ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን ብሪታንያን በብርቱ አስጠነቀቋት፡፡ ፑቲን ብሪታንያ ለዩክሬይን ግዛት ተሻጋሪ ድሮኖችን ከማቀበል ብትቆጠቢ ይሻልሻል ማለታቸው ሬውተርስ ፅፏል፡፡ ቀደም ሲል ታይምስ ጋዜጣ ዩክሬይን በሩሲያ ላይ ግዛት ተሻጋሪ ጥቃት የምታደርሰው በብሪታንያ ስሪት ድሮኖች እንደሆነ መዘገቡ ተጠቅሷ

 
 
 
የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ኢትዮጵያን ጨምሮ በአለም ዙሪያ ከኢነርጂ ደህንነትና ስብጥር ጋር የተገናኘ ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል።

ነሐሴ 12 2018 የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ኢትዮጵያን ጨምሮ በአለም ዙሪያ ከኢነርጂ ደህንነትና ስብጥር ጋር የተገናኘ ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል። እንዲህ አይነት ጦርነት በተነሳ ቁጥር የተቀረው አለም የነዳጅ አቅርቦት የሚስተጓጎል ከሆነ አለም አስተማማኝ የኢነርጂ ምርጫዋ ምን ቢሆን ይበጃል? የሚል ነው ጥያቄው። በ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page