ባለፈው ዓመት የወጣውን የሪል ስቴት አዋጅ ለማስፈፀም የሚያስችል ደምብ ዝግጅት ተጠናቅቆ ወደ ስራ ሊገባ መሆኑ ተነገረ።
- 6 hours ago
- 1 min read
ሚያዝያ 15/2018
ባለፈው ዓመት የወጣውን የሪል ስቴት አዋጅ ለማስፈፀም የሚያስችል ደምብ ዝግጅት ተጠናቅቆ ወደ ስራ ሊገባ መሆኑ ተነገረ።
ይህ የተባለው በዛሬው ዕለት የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤና አዲስ አፍሪካ የተሰኘው የሪል ስቴት ኤግዚቢሽን በተከፈተበት ወቅት ነው።
የሪል ስቴት አዋጅ ማስፈጸሚያ ደምቡን ያዘጋጀው የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር መሆኑንና በአዋጁ የተካተቱ የገዢውንም የአልሚውንም ጥቅም የሚያስጠብቁ አሰራሮችን የሚቀይስ መሆኑን በሚኒስቴር መ/ቤቱ የቤቶች ልማት ጥናት የግል ሴክተር ተሳትፎ ዴስክ ሃላፊ አቶ ታፈሰ ነጋ ነግረውናል።

"አዲስ አፍሪካ" የተሰኘው ይህ የሪል ስቴት ኤግዚቢሽን መዲናዋን የአፍሪካ የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ማዕከል ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል።
ዛሬን ጨምሮ የፊታችን ለ4 ተከታታይ ቀናት በሚቆየው ኤግዚቢሽን የኢትዮጵያ የሪል ስቴት አልሚዎች፣ የኮንስትራክሽን ግብዓት አምራቾች ፣ባንኮችና የፋይናንስ ተቋማት ተሳታፊ ሆነዋል።
ከኤግዚቢሽኑ ጎን ለጎን የሚካሄደው የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤ በቀጠናው ሀገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትስስር፣ የንግድ ልውውጥ እና የፖሊሲ ስምምነት ላይ ያተኮረ ነው።
አዲስ አፍሪካ የሪል ስቴት ኤግዚቢሽን ደግሞ የቤት ልማት ቴክኖሎጂዎችን፣ የኢንቨስትመንት አማራጮችን እና የዘርፉን ተዋናዮች በአንድ ጣሪያ ስር እያገናኘ የሚገኝ መድረክ ነው ተብሏል።
በኤግዚቢሽኑ የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አባላት የሆኑ አልሚዎች ብቻ የሚሳተፉ በመሆኑ፣ ደንበኞች ህጋዊና እውቅና ካላቸው ድርጅቶች ጋር ብቻ እንዲገናኙ እድል የፈጠረ እንደሆነም ተጠቅሷል።
ባንኮችና የፋይናንስ ተቋማት በኤግዚቢሽኑ ላይ መሳተፋቸው፣ ለቤት ፈላጊው ማህበረሰብ የተሻለ የብድርና የክፍያ አማራጭ ለማግኘት አመቺ ሁኔታ ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ኤግዚቢሽኑን የኢትዮጵያ የሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር ከዶክሳ ኢቨንትስ ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል።
ምንታምር ፀጋው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments