top of page

በፊንቴክ ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ወሰነ።

  • 6 hours ago
  • 1 min read

ነሐሴ 2018


በፊንቴክ ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ወሰነ።


የተላለፈው መግለጫ ከዩቲዩብ እንዲወርድ እና ይቅርታ እንዲጠየቅ ፍርድ ቤቱ አዟል።

ዐቃቤ ሕግ አርቲስቶቹ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ መግለጫ በመስጠታቸው የዋስትና መብታቸው ተነስቶ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ያቀረበውን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጎታል።


ዛሬ ነሀሴ 01 2018 ዓ/ም ጠዋት በነበረው ችሎት ተጠርጣሪ አርቲስቶቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ለዐቃቤ ሕግ አቤቱታ በጽሑፍ ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ ለምን መግለጫ እንደሰጡም ለችሎቱ የቃል ማብራሪያ አቅርበዋል።


አርቲስቶቹ በማብራሪያቸው ድርጊቱን የፈጸሙት በማኅበራዊ ሚዲያ ከሚደርስባቸው ስም ማጥፋትና መልካም ስም ከማጉደፍ ራሳቸውን ለመከላከል አስበው እንደሆነ አስረድተዋል።


ጉዳዩን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለከሰዓት 9:00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው ፍርድ ቤቱ፤ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠትና ማብራሪያ ማቅረብ ጥፋት መሆኑን አመልክቷል።


በማኅበራዊ ሚዲያ ለሚጠፋ ስም መልስ ለመስጠት እንኳን ቢሆን ድርጊቱን ፈጽሟል የሚሉትን አካል በሕግ መጠየቅ ሲገባ መግለጫ መስጠቱ ተገቢ እንዳልሆነ ጠቁሟል።


ሆኖም «በጥቃቅን ጥፋቶች የዋስትና መብትን ማገድ ተገቢ ሆኖ አላገኘነውም» ሲል ዐቃቤ ሕግ የተከሳሾች የዋስትና መብት ተነስቶ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።


በተጨማሪም አርቲስቶቹና ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት ድርጊቱን ሆን ብለው የፈጸሙት በመሆኑ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 457 መሠረት እንዲቀጡ፣ ወይም በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ እንዲመሠረትባቸው ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ አልተቀበለውም።


በዚህም መሠረት መግለጫ የሰጡት አርቲስቶች ሌላ ጊዜ ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጽሙ በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ውሳኔ ተሰጥቷል።


በሌላ በኩል «እግረኛው» በተሰኘው የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ እንዲተላለፍ ያደረገው አቶ ተክለሃይማኖት አዳነ ቪዲዮውን ከዩቲዩብ (YouTube) ላይ እንዲያወርድና ይቅርታ እንዲጠይቅ ፍርድ ቤቱ አዟል።


የመደበኛው የሕግ ሂደት ቀጠሮ ለጥቅምት 02 ቀን 2019 ዓ.ም የተቀጠረ መሆኑ ታውቋል።


ገዛ ጌታሁን

Recent Posts

See All
በአገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ ያሉ ቤተ እስራኤላውያን ከምክከሩ በኋላ እውቅና ይሰጠናል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናገሩ፡፡

ነሐሴ 1 2018 በአገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ ያሉ ቤተ እስራኤላውያን ከምክከሩ በኋላ እውቅና ይሰጠናል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናገሩ፡፡ በኢትዮጵያ እስከሁን ድርሶብናል ላሉት "መገለል እና መገፋት "በዓይነትም፣ በገንዘብ ካሣ እንፈልጋለን ሲሉ በኢትዮጵያ የቤተ እስራኤል የልማት ድርጅት ፕሬዚዳንት አቶ በላይነህ ታ

 
 
 
በቅርቡ የፀደቀውን ‘‘የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት አዋጅ‘‘ መመሪያን ባለመተግበር ሳይበር ጥቃት በተቋሙ ላይ የአገልግሎት መቋረጥን፣ የሀገር ደህንነት ማናጋት እና በዜጎች ህይወት ላይ ጉዳት ካደረሰ ሀላፊዎች ወይንም ሰራተኞች ከ7 አመት እስከ 10 አመት ፅኑ እስራት እንደሚቀጡ በአዋጁ መደንገጉ ተነገረ።

ነሐሴ 1 2018 በቅርቡ የፀደቀውን ‘‘የቁልፍ መሠረተ ልማቶች የሳይበር ደህንነት አዋጅ‘‘ መመሪያን ባለመተግበር ሳይበር ጥቃት በተቋሙ ላይ የአገልግሎት መቋረጥን፣ የሀገር ደህንነት ማናጋት እና በዜጎች ህይወት ላይ ጉዳት ካደረሰ ሀላፊዎች ወይንም ሰራተኞች ከ7 አመት እስከ 10 አመት ፅኑ እስራት እንደሚቀጡ በአዋጁ

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page