በአገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ ያሉ ቤተ እስራኤላውያን ከምክከሩ በኋላ እውቅና ይሰጠናል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናገሩ፡፡
- 2 hours ago
- 1 min read
ነሐሴ 1 2018
በአገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ ያሉ ቤተ እስራኤላውያን ከምክከሩ በኋላ እውቅና ይሰጠናል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናገሩ፡፡
በኢትዮጵያ እስከሁን ድርሶብናል ላሉት "መገለል እና መገፋት "በዓይነትም፣ በገንዘብ ካሣ እንፈልጋለን ሲሉ በኢትዮጵያ የቤተ እስራኤል የልማት ድርጅት ፕሬዚዳንት አቶ በላይነህ ታዘብኩ ነግረውናል።
እየተካሄደ በሚገኘው የምክክር ሂደት ላይ እየተሳተፉ ያሉ 26 ቤተ እስራኤላውያን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የነበራቸው ድርሻ በአግባባቡ እንዲሰነድላቸው እና ማንነታቸውም እንዲታወቅላቸው መጠየቃቸውን አስረድተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ቤተ እስራኤላውያን የማንነት እውቅና እና የሃይማኖት መሰል ጥያቄዎቻችን በምክከሩ ይፈታል የሚል ተስፋ አለን ብለዋል አቶ በላይነህ፡፡
ቤተ እስራኤላዊያን ህጋዊ እውቅና ያለው የአምልኮ እና የቀብር ስፍራ እንደሌላቸው የጠቀሱት ፕሬዚዳንት አቶ በላይነህ ታዘብኩ በዚህ ምክንያት የወከሉት መቸገራቸውን ዘርዝረዋል፡፡
ቤተ አስራኤላዊን በእጅ ሙያቸው፣ በሃይማኖታቸው እና በሌላው ማህበራዊ ህወይታቸው ተገለዋል ያሉት አቶ በላይነህ "ቡዳ" ፣"ካይላ"፣" ፉጋ" እና "ቂሌ" እየተባሉ ሰም እየጠሰጣቸው ሲገለሉ ኖረዋል ብለዋል አቶ በላይነህ፡፡
ክምክክሩ በኋላ የማንነት አውቅና ይሰጠናል፣ ህጋዊ የሆነ የአምልኮ እና የቅብር ስፍራም እናገኛለን የሚል ተስፋ አለን ሲሉ የቤት እስራኤል የልማት ድርጅት ፕሬዚዳንት አቶ በላይነህ ታዘብኩ ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ በሁሉም ክልሎች ቤተ እስራኤላዊን አሉብን እናስባለን ያሉት ፕሬዚዳንቱ በማንነታቸው ላይ በሚደርሰው መገለል ግን እራሳቸውን ደብቀው ነው የሚኖሩት ብለዋል፡፡
በዚህም ምክንያት በአሁኑ ወቅት ምን ያክል ቁጥር ያላቸው ቤተ እስራኤላዊን በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ማወቅ አልቻልንም ሲሉ አክለዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ....
ያሬድ እንዳሻው
_edited.jpg)
