top of page

በግጭቶች የቋረጡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ስራ ለማስጀመር ከየአካባቢው አስተዳድሮች ጋር እየተነጋገረ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተናገረ።

  • 3 hours ago
  • 1 min read

ሚያዝያ 14/2018


በተፈጠሩ ግጭቶች ምክንያት የቋረጡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ስራ ለማስጀመር ከየአካባቢው አስተዳድሮች ጋር እየተነጋገረ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተናገረ።


ግጭቶች ባሉባቸው በሁሉም አካባቢዎች 14 የመንገድ ፕሮጀክቶች ተቋርጠው መቆየታቸውን የነገሩን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሃመድ አብዱረህማን የፀጥታው ሁኔታ መሻሻል የታየባቸው አካባቢዎች ያሉ ፕሮጀክቶችን ዳግም ስራ መጀመሩን ነግረውናል።

ቢሊዮን ብር ወጥቶባቸው የተጀመሩ፤ አንዱን ክልል ከሌላው፤ ገጠሩን ከከተማው ጋር ያገናኛሉ ተብለው እየተገነቡ ያሉ የመንገድ ፕሮጀክቶች በሰላም እጦት ምክንያት ግንባታቸው ሲስተጓጎል እንደ ሃገር በብዙ መንገድ ኪሳራን የሚያስከትል ነውና ቀድማችሁ የምትወስዱት እርምጃ አንደምን ያለ ነው? በግንባታው የሚሰማሩ ሰራተኞቻችሁን የስራ ላይ ደህንነት የምታስጠብቁትስ እንዴት ነው? ያልናቸው ዋና ዳይሬክተሩ ችግሩ እንዲስተካከል አፋጣን እርምጃ እንወስዳለን የሚል ምላሽ ሰጥተውናል፡፡


ከዚህም በተጨማሪ የሰላም እጦት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዳይጠናቀቁ ከሚያደርጉ ምክንያቶች አንዱ እንደሆነ የሚያነሱት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሃመድ አብዱረህማን፤ ውጫዊና ውስጣዊ ባሉት ምክንያት የግንባታ ስራቸው የተጓተቱ፤ እርሳቸውን ጨምሮ በአስተዳደራቸው ልዩ ክትትል የሚደረግባቸው 30 የሚደርሱ የመንገድ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ነግረውናል።


ከመካከላቸው 14ቱ የተሻለ የአፈፃፀም ደረጃ ላይ ደርሰዋል ብለዋል፡፡


ለ30 የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ መዘግየት ከተጠቀሱት ምክንያቶች በተጨማሪ መንገዶቹ በሚገነባባቸው አካባቢዎች ያሉ ንብረቶችን የማንሳት(የወሰን ማስከበር) ስራ ለመዘግየታችን ዋናው ምክንያት ነው፤የግንባታ ስራ ተቋራጮችና አማካሪ ድርጅቶች ስራቸውን በአግባቡ አለመስራት የስራ መዘግየት ያመጣል ብለውናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…..


ምንታምር ፀጋው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Recent Posts

See All
ፖሊስ በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት፡፡

ሚያዝያ 14/2018 ፖሊስ በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት፡፡ ፖሊስ ተጨማሪ 14 ቀን ለምርመራ እንዲፈቀድለት ባለፈው አርብ በነበረው ችሎት ጠይቆ ለውሳኔ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ ቀጥሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡ በ"ፊንቴክ"(Finte

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page