በአብዛኞቹ አካባቢዎች ላይ ምርጫ ለማድረግ አስቻይ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን በቀረቡ ሪፖርቶች ተረጋግጧል ሲል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተናገረ፡፡
- 18 minutes ago
- 1 min read
ግንቦት 10/2018
በአብዛኛዎቹ አካባቢዎች ላይ ምርጫ ለማድረግ አስቻይ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን በቀረቡ ሪፖርቶች ተረጋግጧል ሲል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተናገረ፡፡
አሁንም ግን ትኩረት የሚሹ ቦታዎች መኖራቸው ተጠቅሷል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ሥምሪት የሰጣቸው የክትትል ቡድኖች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸውን አካባቢዎች የፀጥታ ሁኔታን በተመለከተ ዝርዝር ሪፖትርት ማቅረባቸውን ባወጣው መግለጫ አስረድቷል፡፡
በአካባቢዎቹ ላይ ያለውን ተጨባጭ የፀጥታ ሁኔታና የፖለቲካ ምኅዳር ክትትል አድርጎ ሪፖርት የሚያቀርብ ቡድን ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም ከቦርዱ የተውጣጣ የክትትል ቡድን አዋቅሮ ሥምሪት መስጠቱን ቦርዱ አስታውሷል፡፡

የሥምሪት ቡድኑም ክትትል ሲያደርግ ቆይቶ ሪፖርቱን ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ለቦርዱና ለባለድርሻ አካላት በልዩ መድረክ አቅርቧል ተብሏል።
በዘጠኝ ቡድን የተዋቀረው የክትትል ቡድን በመድረኩ ሪፖርቱን ያቀረበ ሲሆን፤ በሪፖርቱም ከፀጥታ ሁኔታ በተጨማሪ የየአካባቢዎቹ የፖለቲካ ምኅዳር፣ ፓርቲዎች በነፃነት ተንቀሳቅሰው የምርጫ ሥራቸውን ለመሥራት ምን ያኽል አስቻይ ሁኔታ አለ የሚለውን፣ ለምርጫው ያለው የሕዝብ ተነሣሽነትና የምርጫ ካርድ አወሳሰድ ሁኔታን ጨምሮ በርካታ የምርጫ ነክ ጉዳዮች መዳሰሳቸው ተጠቅሷል፡፡
በሪፖርቱቶቹ በአብዛኛዎቹ አካባቢዎች ላይ ምርጫ ለማድረግ አስቻይ ሁኔታ መኖሩን የተረጋገጠ ቢሆንም፤ አሁንም ትኩረት የሚሹ ቦታዎች መኖራቸው ተነግሯል።
በየትኞቹ አካባቢዎች ምርጫውን ለማድረግ አስቻይ ሁኔታ እንዳለ፣ የትኖች አካባቢዎች ደግሞ ትኩረት የሚሹ እንደሆኑ በቦርዱ መግለጫ ላይ አልተጠቀሰም፡፡

