top of page

በአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ የተሻለ የስራ ዕድል ቢፈጠርም አሁንም ብዙ ቀሪ ስራዎች አሉ ተባለ።

  • sheger1021fm
  • 10 hours ago
  • 1 min read

ህዳር 11 2018


በአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ የተሻለ የስራ ዕድል ቢፈጠርም አሁንም ብዙ ቀሪ ስራዎች አሉ ተባለ።


ዘርፉ ለ200,000 ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠሩ የተነገረ ሲሆን 80 በመቶዎቹ ሴቶች መሆናቸው ተጠቅሷል።


መዋዕለ ነዋይ በማፍሰስ ወደ ዘርፉ ልማት መግባት ለሚፈልጉ ሴቶች ግን አሁንም ሁኔታዎች ብዙም ምቹ አለመሆናቸው ተነግሩዋል፡፡


የመሬትና የብድር አቅርቦት በዘርፉ መሠማራት የሚፈልጉ ሴቶችን ይገጥማሉ ከተባሉ ችግሮች መካከል ናቸው።


ዘርፉ ላይ በአመራር ደረጃ ያሉ ሴቶች ቁጥርም ዝቅተኛ ነው።

ree

የኢትዮጵያ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ አምራቾችና ላኪዎች ማህበር ትኩረቱን በሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ላይ ያደረገ ኮንፈረንስ እያካሄደ ነው።


ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ከ500 ሚሊየን ዶላር በላይ በያመቱ እንደምታገኝ በኮንፈረንሱ ላይ ሲነገር ሠምተናል።


ከሀያ ዓመት በፊት ግን ከዘርፉ ታገኝ የነበረው ገቢ 28.5 ሚሊዮን ዶላር ነው ተብሏል።


ከግብርና ንዑስ ዘርፎች አንዱ የሆነው አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ለኢትዮጵያ የውጪ ምንዛሪ በማስገኘት አራተኛ ደረጃ የሚገኝ መሆኑ ተጠቅሷል።


ግብርና በኢትዮጵያ ከአጠቃላይ ህዝቡ ከ70 በመቶ በላይ ለሚሆኑት ቀጥተኛ የስራ ዕድል የፈጠረ መስክ መሆኑ ተነግሯል።


ከእነዚህ መካከል ደግሞ 53 በመቶዎቹ ሴቶች ናቸው ተብሏል።


ንጋቱ ረጋሳ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page