top of page

በሆንግ ኮንግ በመኖሪያ ሕንፃዎች በደረሰ የቃጠሎ አደጋ በጥቂቱ 55 ሰዎችን መግደሉ ተሰማ፡፡

  • sheger1021fm
  • 4 minutes ago
  • 1 min read

የህዳር 18 2018


በሆንግ ኮንግ በመኖሪያ ሕንፃዎች በደረሰ የቃጠሎ አደጋ በጥቂቱ 55 ሰዎችን መግደሉ ተሰማ፡፡


በአደጋው ሕይወታቸው ማለፉ ከተረጋገጠው ሌላ 279 ሰዎች ደግሞ የደረሱበት እንዳልታወቀ CNN ፅፏል፡፡


ቃጠሎው እስከ ቅርብ ሰዓት በቁጥጥር ስር አልዋለም ተብሏል፡፡

ree

በፍጥነት የተዛመተው ቃጠሎ በ7 ሕንፃዎች ላይ ጉዳት ማድረሱ ታውቋል፡፡


የቃጠሎው መንስኤ ምን እንደሆነ የታወቀ ነገር የለም፡፡


ለጥገና አጋዥነት የተተከሉ ቀርክሃ ስሪት የህንፃ መወጣጫዎች ቃጠሎውን አባብሰውታል ተብሏል፡፡


የግዛቲቱ አስተዳደር ለእዳ ቅነሳ ሲባል በመንግስት ፕሮጄክቶች የቀርክሃ የህንፃ መወጣጫዎች ስራ ላይ እንዳይውሉ ማድረጉን መረጃው አስታውሷል፡፡


ከአሁኑ አደጋ ጋር በተያያዘ 3 ሰዎች መታሰራቸው ተሰምቷል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page