በ2015 የትምህርት ዘመን ወደ ትግበራ የገባውን እና አዲሱን ስርዓተ ትምህርት የያዘው መፀሀፍ ህትመት ከምን ደረሰ?
- sheger1021fm
- 1 hour ago
- 1 min read
ጥር 15/2018
የኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት ካለበት ችግር እንዲወጣ እና ውጤታማ እንዲሆን ታስቦ ከተከወኑ ስራዎች አንዱ የትምህርት ስርዓቱን ማሻሻል ነው፡፡
ዘርፉን ያሻሽላል የተባለለት አዲሱ ስርዓተ ትምህርት ተቀርፆ ወደ ትግበራ ከገባ 4 ዓመታትን አስቆጥሯል።

በ2015 ዓ.ም ተሻሽሎ ወደ ትግበራ የገባው የትምህርት ስርዓትም አዳዲስ የመማሪያ እና ማስተማሪያ መፃህፍት ይዞ መጥቷል፡፡
ነገር ግን በዚህ አራት ዓመታት ውስጥ አዲሱን ስርዓተ ትምህርት የያዘው መፀሀፍ እስካሁን ሙሉ ለሙሉ ተማሪዎች እጅ ላይ አለመግባቱም ይነገራል።
በተለይ ደግሞ የሰላም እጦት በነበሩባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች ያሉ ተማሪዎች አዲሱን ስርዓተ ትምህርት የያዘውን መፅሀፍ ለማግኘት መቸገራቸው ተደጋግሞ ሲነሳ ቆይቷል፡፡
ሸገር ሬድዮም በ2015 የትምህርት ዘመን ወደ ትግበራ የገባውን እና አዲሱን ስርዓተ ትምህርት የያዘው መፀሀፍ ህትመት ከምን ደረሰ? ሲል ጠይቋል፡፡
ሙሉ ዘገባወን ያድምጡ…
ፋሲካ ሙሉወርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…..
YouTube : https://url-shortener.me/2DTR
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://url-shortener.me/2DTY
WhatsApp :https://url-shortener.me/2DU0
Website፡ https://www.shegerfm.com/
LinkedIn :https://url-shortener.me/2DU8
Tiktok : https://url-shortener.me/2DUB
Instagram : https://url-shortener.me/2DUD












Comments