top of page

ሰኔ 8፣ 2016 - ኢትዮጵያ 150 ጊጋ ዋት በላይ እምቅ የኢነርጂ ሀይል ቢኖራትም፤ እስካሁን የመነጨው ሀይል ግን 5.4 ጊጋ ዋት ብቻ ነው ተባለ፡፡

  • Jun 15, 2024
  • 1 min read

ኢትዮጵያ 150 ጊጋ ዋት በላይ እምቅ የኢነርጂ ሀይል ቢኖራትም፤ እስካሁን የመነጨው ሀይል ግን 5.4 ጊጋ ዋት ብቻ ነው ተባለ፡፡


ይህን ያሉት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ዋሌ(ዶ/ር) ናቸው፡፡


ሚኒስትር ድኤታው ምክንያታዊው የናይል ወንዝ አጠቃቀምና ቀጠናዊ ውህደት ዓመታዊ ፎረም ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያ ያላትን የሀይል እምቅ ሀብት መጠቀም ያልቻለችው መስኩ በጣም ከፍተኛ የሆነ መዋዕለ ነዋይ የሚጠይቅ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡


ዛሬ በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል የአባይ ተፋሰስ ሀገራት የውሃ ሀብትን በጋራ እና በፍትሃዊነት መጠቀም ስለሚችሉባቸው መንገዶች ላይ የሚመክሩበት የ’’አፍሪ ራን’’ ሶስተኛው ጉባኤ እየተካሄደ ነው፡፡

የጉባኤው አላማን የተመለከተ ሚኒስትር ድኤታ ኢንጅነር ሱልጣን ዋሌ፤ በዋናነት 14 ዓመት የሞላውን የኮፕሬሲፍ ፍሬም ወርክ ስምምነት የት እንደደረሰ ለመገምገም ያለመ ነው ብለዋል፡፡


ስምምነቱ የውሃ አጠቃቀም እና አስተዳደር ላይ የሚመለከቱ ጉዳዮችን ያቀፈ ሰነድ መሆኑ አስረድተዋል፡፡


ሌላው አላማው የሀይል ትስስር ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም ቀጠናውን በሀይል ለማስተሳሰር ያለመ ነው ያሉ ሲሆን ከፍተኛ ያለመረጋጋት የሚታይበትን የተፋሰሱን ሀገራት በሀይል ለማስተሳሰር የሚያስችል ውይይት ይደረግበታል ብለዋል፡፡


እስካሁንም ኢትዮጵያ፤ ለ10 ዓመት ያክል ለጅቡቲ፣ ለ8 ዓመት ያክል ለሱዳን፣ ለኬኒያ ላለፉት 2 ዓመታት ኤሌክትሪክ ሀይል እያቀረበች ነው፡፡


ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ ብቸኛዋ ያውም በዝቅተኛ ኤሌክትሪክ ታሪክ፤ ሀይል እያቀረበች ያለች ሀገር ነች ሲሉ ሚኒስትር ድኤታው አስረድተዋል፡፡


ሶስተኛው ደግሞ ታላቁ ህዳሴ ግድቡን ለልማትና ለትስስር እንዴት እንጠቀም በሚል ጉዳይ ላይ ጉባኤው ይመክራል ብለዋል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Recent Posts

See All
ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡

ሐምሌ 21 2018 ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡ የዓሣ ምርቱ ወደ መሃል ሃገር እየተጫነ ለአዲስ አበባ ገበያ እየቀረበ ነውም ተብሏል፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ መገንባቱን ተከትሎ በተፈጠረው ንጋት ሰው ሰራሽ ሃይቅ በኢትዮጵያ ትልቁና ከ70 በላይ ደሴቶች ያሉት የውሃ አካል ነው፡፡ ከቅርብ

 
 
 
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ።

ሐምሌ 20 2018 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ። እቅዱ የኔትወርክ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ፣ የሰብስቴሽን እና ተያያዥ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች፣ ስማርት ግሪድ እና ቆጣሪ ማስፋፋትን እንደሚያካትት አገልግሎቱ ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page