ሰኔ 6 2017 - የእስራኤል ጦር በኢራን ላይ ከባድ ድብደባ ፈፅሜያለሁ አለ
- sheger1021fm
- 2 days ago
- 1 min read
የእስራኤል ጦር በኢራን ላይ ከባድ ድብደባ ፈፅሜያለሁ አለ፡፡
ጦሩ ድብደባዬ በኢራን የኒኩሊየር ተቋማት ላይ ያነጣጠረ ነው ማለቱን ቢቢሲ ፅፏል፡፡
አብዮታዊ ዘብ የተሰኘው የኢራን የጦር ክፍል አዛዥን ሁሴን ሰላምን ገድያለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡
ሌሎች የኢራን የጦር አዛዦችም በድብደባው መገደላቸው ታውቋል፡፡

የኢራን መንግስታዊ ቴሌቪዥን፤ እስራኤል በመኖሪያ አካባቢዎች ላይ በፈፀመችው ድብደባ ሕፃናትን ጨምሮ ሰላማዊ ሰዎችን ገድላብናለች ሲል ዘግቧል፡፡
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ኢራን ለእስራኤል ሕልውና እጅግ አደገኛ ሀገር ነች ማለታቸው ተሰምቷል፡፡
እስራኤል የአፀፋው ጥቃት ሊሰነዘርባት እንደሚችል ገምታለች፡፡
በዚህም የተነሳ የአስቸኳይ ጊዜ ስራ ላይ ማዋሏ ታውቋል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Comentários