ሰኔ 6 2017 - በኮሜሳ የዳኞች ሹመት ዙሪያ የቀረበው ክርክር ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በስራቸው ላይ ለመቆየት በሙሉ ድምፅ መስማማታቸው ተሰማ
- sheger1021fm
- Jun 13
- 1 min read
በኮሜሳ የዳኞች ሹመት ዙሪያ በኢትዮጵያዊው ጠበቃ በቀረበ ክስ ምክንያት የስራ ጊዜያቸው ያበቃ ዳኞች፤ የቀረበው ክርክር ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በስራቸው ላይ ለመቆየት በሙሉ ድምፅ መስማማታቸው ተሰማ።
የኮሜሳ ፍርድ ቤት በምስራቃዊ እና ደቡባዊ አፍሪካ ባሉ አባል ሀገራት ውስጥ የንግድ ስምምነቶችን እና ታሪፍን ጨምሮ የሚነሱ ውዝግቦች የሚዳኙበት እና ኮሜሳ ካሉት አስራ አንድ ተቋማት መሀከል አንዱ ነው።
የኮሜሳ ፍርድ ቤትን የዳኞች ምልመላ ሂደትን በመቃውም ክስ የመሰረቱት ኢትዮጵያዊው ጠበቃ አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው የፓን አፍሪካ የጠበቆች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ናቸው።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…
የኔነህ ሲሳይ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il












Comments