top of page

ሰኔ 4፣ 2016 - የአካል ጉዳተኞች በሀገራዊ ምክከሩ ጉዳያቸዉ እንዲደመጥ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጠየቀ፡፡

  • Jun 11, 2024
  • 1 min read

የአካል ጉዳተኞች በሀገራዊ ምክከሩ ጉዳያቸዉ እንዲደመጥ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጠየቀ፡፡


ኢትዮጵያ በምታካሄደው አገራዊ ምክክር ላይ የአከል ጉዳተኞች ጥያቄዎች እንዲደመጡም መፍትሄም እንዲያገኙ ኢሰመኮ ጠይቋል፡፡


አካል ጉዳተኞች በምክክሩ ላይ ትርጉም ያለዉ ተሳትፎ እንዲያደርጉ አፈልጋለሁ ሲል ኮሚሽኑ አስረድቷል፡፡


በኮሚሽኑ የሴቶች የህጻናት የአረጋውያን እና የአክል ጉዳተኞች መብቶች ኮሚሽነር ርግበ ገብረሐዋሪያ፤ በሰጡት ምክረ ሀሳብ የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ ማረጋገጥ ከመንግስት ይጠበቃል፤ በምክከሩ መሳተፍ ደግም የአካል ጉዳተኞች መብት ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡


የአካል ጉዳተኞች በማህበራቸው እና በተወካዮቻቸው በኩል መፍትሄ ያስፈልገዋል ያሉትን ጉዳይ ለምክክሩ እንዲቀርቡም ተጠይቀዋል፡፡


ኮሚሽነር ርግበ ከግጭት እና ጦርነት ጋር የተያያዙ ጉዳይዎችም ሆኑ ከግጭት አዉድ ዉጭ የሆኑ አካል ጉዳተረኖች እንዲመለሱላቸዉ የሚፈልጉትን ጥያቄዎች በአግባቡ ከተወከሉና ትርጉም ባለዉ መልኩ ከተሳተፉ ጥያቄዎቸቻቸዉ አጀንዳ ሊሆንላቸዉ እንደሚችል አስረድተዋል፡፡


የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ የምናረጋግጠዉ ጥያቄዎቻቸዉ በአጃንዳዎች ዉስጥ በመካተታቸዉ ነዉም ብሏል ኮሚሽኑ፡፡


የአካል ጉዳተኞች መሃበራት እና አካል ጉዳተኞች ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች ከምክክር ኮሚሽኑ ጋር በቅርበት እንዲሰሩም ተጠይቋል፡፡


ያሬድ እንዳሻው



Recent Posts

See All
ዛሬ ብሔራዊ ባንክ ይፋ ባደረገው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ161 ብር ከ79 ሳንቲም መሸጡ ተነገረ፡፡

ነሐሴ 6 2018 ዛሬ ብሔራዊ ባንክ ይፋ ባደረገው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ161 ብር ከ79 ሳንቲም መሸጡ ተነገረ፡፡ ዛሬ ይፋ በሆነው ጨረታ 125 ሚሊዮን ዶላር ለጨረታ ቀርቧል ተብሏል፡፡ በጨረታው 28 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን በጨረታው የድርሻቸውን ተጫርተው የወሰዱ ባንኮች ቁጥር 9 መሆ

 
 
 
ብሔርን መሰረት ያደረገው የክልሎች አወቃቀር ይቀጥል በሚለው የ500 ቡድን የሀገራዊ ምክክር ተመካካሪዎች ተስማምተዋል፡፡

ነሐሴ 6 2018 ብሔርን መሰረት ያደረገው የክልሎች አወቃቀር ይቀጥል በሚለው የ500 ቡድን የሀገራዊ ምክክር ተመካካሪዎች ተስማምተዋል፡፡ አገሪቱ የምትከተለው የመንግስት ሥርዓት ምን ይሁን? ለሚለው ተመካካሪዎቹ ኢትዮጵያ በፕሬዚዳንት ትመራ በሚለው ላይ ሙሉ ለሙሉ ተስማምተዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ከየት ይመረጥ? ሥርዓቱ ፓር

 
 
 
የነሐሴ 6 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ደቡብ_አፍሪካ በደቡብ አፍሪካ በአንድ የማዕድን ዝቃጭ ማስወገጃ ስፍራ መደርመስ 14 ሰዎች የሞቱበት አደጋ እየተመረመረ ነው ተባለ፡፡ ሌሎች 8 ሰዎች ደግሞ አካላዊ ጉዳት እንደገጠማቸው ቢቢሲ ፅፏል፡፡፡ በዝቃጩ ውስጥ የተቀበሩ ሌሎች ሰዎች ሳይኖሩ አይቀሩም ተብሏል፡፡ በአደጋው የሞቱት እና አካላዊ ጉዳት የገጠማቸው ሕ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page