top of page

ሰኔ 26፣ 2016 - ሀገርን ከፍተኛ አደጋ ላይ የሚጥለውን የኬሚካል ክምችት ለማስወገድ ምን እየተሰራ ይሆን?

  • sheger1021fm
  • Jul 3, 2024
  • 1 min read

የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው እንደ ዲዲቲ ያሉ ኬሚካሎች ክምችት ሳይወገድ በቆየ ቁጥር፤ በአካባቢና ህይወት ባላቸው ላይ ሁሉ የሚያስከትለው አደጋ ከፍተኛ መሆኑ ይነገራል።


ከዓመታት በፊት ከ 1,300 ቶን በላይ የዲዲቲ ክምችት መኖሩ ተነግሮ ነበር።


ከቅርብ ዓመታት ወዲህ 450 ቶን ያህሉ እንዲወገድ መደረጉን ሰምተናል።


ይሁንና አሁንም የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው ኬሚካሎች ክምችት ስጋት እንደፈጠረ መሆኑ ይነገራል።


ለመሆኑ ሀገርን ከፍተኛ አደጋ ላይ የሚጥለውን የኬሚካል ክምችት ለማስወገድ ምን እየተሰራ ይሆን?


በህገወጥ መንገድ የሚገቡትን እና ጊዜ ያለፈባቸውን ኬሚካሎች የመቆጣጠሩ ስራስ ምን ያህል ውጤት እያመጣ ነው ?


በዚህ ጉዳይ ላይ የሚመለከተውን አካል ጠይቀናል።


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page