ሰኔ 23 2017 - የህግ ባለሞያና ጠበቃ አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው የአፍሪካ የጠበቆች ማህበራት ህብረት ም/ቤት ፕሬዘዳንት ሆነው መመረጣቸው ተሰማ
- sheger1021fm
- Jun 30
- 1 min read
በአይቮሪኮስት አቢጃን በተካሄደው 15ኛው የአፍሪካ የጠበቆች ማህበራት ህብረት መደበኛ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያዊው የህግ ባለሞያና ጠበቃ አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው የአፍሪካ የጠበቆች ማህበራት ህብረት ም/ቤት ፕሬዘዳንት ሆነው መመረጣቸው ተሰማ፡፡
የጠበቆች ማህበራት ህብረት ም/ቤት ባካሄደው ስብሰባው አቶ ቴዎድሮስን ለፕሬዘዳንትነት የመረጠው ከአባል ሀገራቱ መካከል ከ3/4ኛ በላይ ድምጽ በማግኘት መሆኑን ሰምተናል፡፡

የአፍሪካ የጠበቆች ማህበራት ህብረት 54ቱን የአፍሪካ ሀገራት በአባልነት የያዘ እና 8 አካባቢያዊ ተቋማትን በአባልነት በመያዝ ግዙፍ የሞያ ማህበር ም/ቤት መሆኑ ይነገራል፡፡
ለመጪዎቹ 3 ዓመታት ም/ቤቱን እንዲመሩ የመረጡት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው የመጀመሪያው ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆኑ ከምስራቅ አፍሪካ ቀጠናም ፓሉን እንዲመሩ የሆኑ የመጀመሪያው ሰው ናቸው ተብሏል፡፡
በአቢጃን በተደረገው 15ኛው የአፍሪካ የጠበቆች ማህራት ህብረት ም/ቤት ስብሰባ ከፕሬዘዳንቱ በተጨማሪ ሌሎች የስራ አስፈፃሚ አባላትና አምስት ምክትል ፕሬዘዳንቶች ከአፍሪካ የተለያዩ አካባቢዎች መመረጣቸውንም ሰምተናል፡፡
የኔነህ ሲሳይ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il








