ሰኔ 20 2017 - በአዲስ አበባ ከተማ የደንብ ጥሰት በ69.8 በመቶ ቀንሷል ተባለ።
- sheger1021fm
- 1 day ago
- 1 min read
በሌላ በኩል የደንብ ጥሰቶችን ፈፅመው ከተገኙት ውስጥ ከ300 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ተናገረ።
በአዲስ አበባ የደንብ ጥሰት ከፈፀሙ ሰዎች በተያዘው በጀት ዓመት 11 ወራት የተሰበሰበው ቅጣት ከ300 ሚሊየን ብር በላይ ሲሆን ከግለሰቦች እና ከተቋማት የተሰበሰበ ነው ተብሏል፡፡
ይህንን የሰማነው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የበጀት ዓመቱን እቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና ውይይት ባካሄደበት ወቅት ነው።
በተለይ የኮሪደር ልማቱን እና የወንዝ ብክለትን መቀነስ ላይ ትኩረት ሰጥቼ እየሰራሁበት ነው ያለው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከእነዚህ እና ሌሎች የደንብ ጥሰቶች 397.6 ሚሊየን ብር መሰብሰቡን ተናግሯል።
በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ከ3,000 በላይ ህገ-ወጥ ግንባታዎችና አስቁሚያለሁ ያለው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከ38,000 በላይ ህገ-ወጥ ጎዳና ላይ ነጋዴዎችን ቀጥቻለሁ ብሏል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
ፋሲካ ሙሉወርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Comments