ሚያዝያ 23 2017 - ''የግል የሎጀስቲክስ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሚያነሱትን ጥያቄ ለመመለስ እየሰራሁ ነው'' የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚ/ር
- sheger1021fm
- May 1
- 1 min read
የወጪ ንግድ ገቢን ለማቀላጠፍ፤ የግል የሎጀስቲክስ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሚያነሱትን ጥያቄ ለመመለስ እየሰራሁ ነው ሲል የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ተናገረ፡፡
የመንግስትና የግሉ የሎጀስቲክስ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዘርፉን ለማቀላጠፍ በጋራ መስራት እንዳለባቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተናግሯል፡፡

እነዚህ የግሉ የሎጀስቲክስ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሚያነሱ ጥያቄ ቢኖርም ችግሩ መፍትሄ እንዲያገኝ በጋራ መስራቱ የሚበጅ ነው ተብሏል፡፡
በዘርፉ ረጅም ዓመት ያስቆጠሩ ተቋማት እንዳሉ ሁሉ ለአዳዲሶቹ ድርጅቶችም እየሰሩ ላሉት ስራ እውቅና መስጠት እንደሚያስፈልግ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ ተናግረዋል፡፡
በግሉ ዘርፍ እያቀላጠፉ ያሉ ተቋማት ከፖሊሲ አኳያ የፋይናንስና የመሬት አቅርቦት ችግር ካለ ለመፍታት ዝግጁነን ሲሉ ሚኒስቴር ዴኤታው አስረድተዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአፍሪካ የነፃ ንግድ ቀጠና ላይ ምርቶቿን ይዛ ለመሳተፍ የግሉና የመንግስት አገልግሎትን ማቀላጠፍ አስፈላጊ ነው ተብሏል፡፡
ይህ ደግሞ በመንግስት ብቻ የሚሸፍን ባለመሆኑ የግሉን ዘርፍ በማሳተፍ ጥያቄዎቻቸውን በመመለስ ስራውን ማስቀጠል እንደሚያስፈልግም ተነግሯል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. https://www.mixcloud.com/ShegerFM/frger/
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r












Comments