top of page

ሚያዝያ 22 2017 - እናት ባንክ “ለእናቴ” የፅሁፍ ውድድር ከአዕምሯዊ ጥበቃ ባለስልጣን የባለቤትነት ማረጋገጫ ማግኘቱን ተናገረ፡፡

  • sheger1021fm
  • Apr 30
  • 1 min read

እናት ባንክ ከአምና ጀምሮ እያካሄደ ያለው “ለእናቴ” የፅሁፍ ውድድር ከአዕምሯዊ ጥበቃ ባለስልጣን የባለቤትነት ማረጋገጫ ማግኘቱን ባንኩ ተናገረ፡፡


“ለእናቴ” የፅሁፍ ውድድር ሰዎች ስለ እናቶቻቸው ጊዜ ሰጥተው እንዲያስቡ፣ እንዲፅፉ እና ተወዳድረው እንዲሸለሙ የሚያደርግ የእናት ባንክ ፕሮግራም ነው፡፡


ይህ የፅሁፍ ውድድር ትላንት ምሽት ለሁለተኛ ጊዜ ተካሂዷል፡፡


በውድድሩ አንደኛ ለወጣው 150 ሺህ ብር፣ ሁለተኛ ለወጣችው 125 ሺህ፣ ሶስተኛ ለወጣው ደግሞ 100 ሺህ ብር ተሸልመዋል፡፡

ree

አራተኛ ለወጣው 75 ሺህ ብር እንዲሁም አምስተኛ ለወጣው ደግሞ 50 ሺህ ብር ተሸልመዋል፡፡


ከ1ኛ እስከ 5ኛ የወጡ ተወዳዳሪዎች የተወዳሩበት ፅሁፍ መፅሄት ላይ ታትሞላቸዋል፡፡

ree

የዓመቱ ድንቅ እናት በሚልም ወ/ሮ የኔነሽ ፍሪሳ መርደሳ የተባሉ እናት የተመረጡት ሲሆን የ200 ሺህ ብር የእናት ባንክ አክሲዮን ተሰጥቷቸዋል፡፡


ይህ የእናት ባንክ ለእናቴ ሲል የጠራውና ትናንት ምሽት ለሁለተኛ ጊዜ የተካሄደው ፕሮግራም የባለቤትነት ማረጋገጫ እንዳገኘ የባንኩ ፕሬዘዳንት አቶ ኤርሚያስ አንዳርጌ አስረድተዋል፡፡


ይህም ውድድር መካሄዱን እንዲቀጥል ያግዛል ብለዋል፡፡


ውድድሩ እናትነት መግለፅ መሆኑንን ያስረዱት ፕሬዘዳንቱ በዚህም "የውድድሩ ተሳታፊዎች እናትነትን ከፍ ስላደረጋችሁ አመሰግናለሁ" ብለዋቸዋል፡፡


እናት ባንክ የሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተለያዩ መላዎች ስራ ላይ ማዋሉን አስረድቷል፡፡

ree

ከእነዚህ መካከልም ከባንኩ አጠቃላይ ትርፍ ከ3 እስከ 5 በመቶ እየተቀነሰ ማስያዣ ማቅብ ለማግይችሉ ሴቶች ብድር እንደሚሰጥ ተናግሯል፡፡


ባንኩ ቅርንጨፎቹንም የሚሰይመው ለሀገራቸው እና ለሴቶች የጎላ ስራ በሰሩ ሴቶች ሰም እንደሆነ አስታውሶ በቅርቡም ሁሉንም እናቶች የሚወክል “እማዬ” የተሰኘ ቅርንጫፍ መክፈቱ ይታወሳል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…






Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page