top of page

ሚያዝያ  22፣2016 - የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከማስተር ካርድ ጋር ተፈራረመ

  • sheger1021fm
  • May 1, 2024
  • 1 min read

የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ወደ ውጭ ሀገር የሚጓዙ ደንበኞቹ  የውጭ ምንዛሪ  በቀላሉ በካርድ ማግኘት እንዲችሉ ከማስተር ካርድ ጋር ተፈራረመ።


የቅድመ ክፍያ ማስተር ካርድ አገልግሎት ወደ ውጭ ሀገር ለሚሄዱ ሰዎች በሚሄዱበት ሀገር የሚያስፈልጋቸውን ገንዘብ በካርዳቸው ላይ በውጭ ምንዛሬ የሚሞላለቸው እና ምንዛሬውን ደግሞ በብር የሚከፍሉበት ነው ተብሏል።


ተጓዦች በሄዱበት ሀገር ሁሉ መጠቀም የሚያስችል ነው ሲባል ሰምተናል።


በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው ማስተር ካርድ እንደ ሀገር ያለውን የውጭ ምንዛሬ ጥሬ ገንዘብ ችግር በመቅረፍ ረገድ አስተዋጾ ያለውና የውጭ ጥሬ ገንዘብ ሸከምን የሚያስቀር ነው ተብሎለታል፡፡


የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከዚህ በተጨማሪ  "ኮፕ ባንክ ኮሚኒቲ ፖስ " የተባለ አገልግሎት ከማስተር ካርድ ጋር በመሆን መጀመሩን ተናግሯል።

ree

ይህ አገልገሎት ጥሬ ገንዘብን በማንቀሳቀስ የሚከናወነውን ተለምዷዊውን አሠራር በማስቀረት፣ የአርሶ አደሮችን መረጃ በኅብረት ሥራ ማህበራት በኩል በማቀናጀት፣ ኢንተርኔት በሌለበት ቦታ እንኳ አርሶ አደሮችንና ማህበራቱን የምርት ግብዓት፣ የግብርና ምርትና የፋይናንስ አገልግሎት በዲጂታል ስልት ማስተሳሰር  የሚያስችል ነው ተብሏል።


ይህም የገጠሩን ማህበረሰብ ለፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ እንዲሁም ዲጂታል ሽግግርን ማላመድን  ከፍተኛ ድርሻ እንደሚኖረው  ባንኩ አስረድቷል።


ባንኩ ባሁኑ ወቅት በመላው ሀገሪቱ 51,000 አርሶ አደሮች፣ 66 የኅብረት ሥራ ማህበራትና 7 ዩኒየኖችን በመመዝገብ ሥራው መጀመሩን ተናግሯል።


በዚህም 9200 ግብይቶችን በማከናወን 1.4 ሚሊዮን ዶላር  ምንዛሬ ያለው ገንዘብ በኅብረት ሥራ ማህበራትና በአርሶ አደሮች መሀከል ተንቀሳቅሷል ብሏል።


ባንኩ አገልግሎቱን በማስፋት የቡና፣ የገብስ፣ የስንዴና የዶሮ እርባታ የዕሴት ሰንሰለት ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ዕቅድ እንዳለው ጠቅሷል።


በዛሬው ዕለት ሥራ ላይ የዋሉት አገልግሎቶች ለ አምስት ዓመት የሚቆየውን በየኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ እና በማስተር ካርድ መሀከል በተደረገው ስትራቴጂካዊ ስምምነት ሊተገበሩ ከታቀዱት የመጀመሪያዎቹ ናቸው ተብሏል።


ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Recent Posts

See All
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።

ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው  ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page